Get Mystery Box with random crypto!

ጵራቅሊጦስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ peraclete — ጵራቅሊጦስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ peraclete — ጵራቅሊጦስ
የሰርጥ አድራሻ: @peraclete
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 577
የሰርጥ መግለጫ

“እግዚአብሔር ይላል፦ በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ”
— ሐዋርያት 2፥17

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-18 22:15:02 ኪዳነ ምሕረት ኢየሱስ ነው።

ኪዳነ ምሕረት ቃሉ የግዕዝ ሲሆን ትርጉሙም የምሕረት ውል ማለት ነው።አዲሱ ኪዳን እግዚአብሔር እኛን ሊምረን ቃል የገባበት ኪዳን ስለሆነ የምሕረት ውል/ኪዳነ ምህረት/ ይባላል።በአዲስ ኪዳን ሞት የሚገባን ምህረትን አግኝተናል።ባለ ዕዳዎቹ በነጻ ተለቀናል።”ሕዝቤ ያልሆነውን ሕዝቤ ብዬ፥ ያልተወደደችውንም የተወደደችው ብዬ እጠራለሁ”ሮሜ 9፡12 በአዲሱ ኪዳን እግዚአብሄር ሰዎችን ሁሉ ሊምር ቃል ገባ እንዲህ ሲል”ዓመፃቸውን እምራቸዋለሁና፥ ኃጢአታቸውንም ደግሜ አላስብም”ዕብ 8፡12 አባታችን እግዚአብሔር እኛን ሊምረን እና ሊቀበለን ቃል የገባው እኛ መልካሞች ስለሆንን ሳይሆን መድሐኒአለም እኛን ወክሎ ስለሞተ ነው።ምህረትን የተቀበልነውና የምንቀበለው በኢየሱስ ምክንያት ነውና በደሙ ኪዳነ ምህረት/የምሕረት ውል/ ቆመልን እንላለን።”ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው”።ማቴ 26፡28

በክርስቶስ በኩል ከሆነው ኪዳን በኋላ እግዚአብሔር ሌላ ኪዳን እንደሰጠ አንዳንዶች ቢያስተምሩም በፍጹም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንዳልሆነ ገልጸን እንናገራለን።ከብሉይ ኪዳን ቀጥሎ ሁለተኛ ኪዳን ያስፈለገው የመጀመሪያው ኪዳን ደካማ ስለነበረ እንደሆነ እናውቃለን።”ሕጉ ምንም ፍጹም አላደረገምና፥ ስለዚህም የምትደክም የማትጠቅምም ስለሆነች የቀደመች ትእዛዝ ተሽራለች፥ ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ገብቶአል”።ዕብ 7፡18 የተሻለ ኪዳን በመምጣቱ የመጀመሪያው ውል አለፈ ፣ተፈጸመ፣ ተሻረ።”አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቷል”ዕብ 8፡13 በጌታችን ኢየሱስ ደም ከተመሰረተው ኪዳን በኋላ ሌላ ኪዳን አለ ካልን አዲሱ ኪዳን እንደ ብሉዩ ጎዶሎ አለው እያልን እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል።ይህ ደግሞ የመጨረሻው ስህተት ነው።አዲሱ ኪዳን ጉድለት ስለሌለው እግዚአብሔር ሰዎችን የሚምርበት ሌላ ቃል ኪዳን ለስዎችም ሆነ ለቦታ አልሰጠም።በጸሐይ ሻማ ማብራት ያስፈልጋል?

በደምህ ኪዳነ ምህረት ያደረክልኝ ኢየሱስ ስምህ ይመስገን።
479 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 21:01:58 ትልቅ ጥያቄ
አንዳንድ ሰዎች ጌታ ኢየሱስ ዛሬም መስቀል ላይ በሰራው ስራ ካማለደ ሌላ አማላጅ ለምን አስፈለገ ብለው ይጠይቃሉ?መልሱ ግልጽ ነው።ሌላ አማላጅ አያስፈልግም!እግዚአብሔር የተቀበለውና ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሆን የምልጃ ስራን የሰራው ኢየሱስ ብቻ ነው።ከእርሱ ውጪ ማማለድ የሚችል ቢኖር እሱ ለምን ሞተ?መጽሐፍ ቅዱስ ዛሬም አማላጅ ነው የሚለው ኢየሱስን ብቻ ነው። "የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው"።ሮሜ 8:34

አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኃላ አያማልድም ይላሉ።እነዚህ ሰዎች ኢየሱስ የሚያማልደው ባቀረበውና ዛሬም ትኩስ በሆነው ህያው መስዋዕቱ በኩል መሆኑን አያስተውሉም።ምልጃው በዘመን ከቆመ ከብሉዩ ካህን በምን ተለየ?እርሱ ዛሬም ብቸኛው አስታራቂ ነው።ቃሉ እንዲህ ይላል"ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።"ዕብ 7:25

ከለመድነው ትምህርት ጋር ሳይሆን ከቃሉ ጋር ሆነን ኢየሱስ ወደ አብ የሚያስገባ ብቸኛው አማላጅ ነው ብለን እንመሰክራለን።

ተበድሎም አማላጅ የሆነው ኢየሱስ ፍቅሩ ምንኛ ድንቅ ነው?እስከ ሞት ለወደደን ምስጋና ይሁን።
357 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-16 22:26:40 ኢየሱስ ብቸኛው አማላጅ ነው!

የዚህ ጽሁፍ ርዕስ ካላስደነገጣቹ መንፈስ ቅዱስ የቃሉን ፍቺ አብርቶላቹሀል ማለት ነውና ስሙ ይመስገን።

የካህን ስራው ማማለድ ነው።ጌታ ኢየሱስ በሌዊ ሳይሆን በመልከ ጸዴቅ ስርአት ካህን ነው።ምን ማለት ነው? ሌዊ ሲሞት ክህነቱ ይሻራል።ኢየሱስ ግን ሞቶ ስለተነሳ የማይሻር የዘላለም ክህነት አለው።"አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ብሎ ይመሰክራልና።"ዕብ 7:14 አስተውሉ!ቃሉ የሚለው "ለዘላለም" ነው።ይሄ ማለት የማማለድ ስራው ዛሬም ህያው ነው።ኢየሱስ ዳግመኛ ሲመጣ ይፈርዳል።አሁን ግን በእምነት ወደሱ ለሚመጡ ሁሉ "እኔ ሞቼላቸዋለውና ምህረት ይገባቸዋል" እያለ ስለ እኛ ይማልዳል።"ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፥ ።"ዕብ 8:1 በሰማይ የማማለድ አገልግሎት ያለው ኢየሱስ ብቻ ነው።

እሱ ለማማለድ ካልከበደው እኛ በእሱ ለመማለድ አይከብደንም።ራስህን ሰውተህ ያማለድከኝ ቤዛዬ ብቻህን በቂዬ ነህ።ተባረክ!
352 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-15 21:31:03 በጎ መአዛዬ
ኖህ ከጥፋት ውሀ በኃላ ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቀረበ።እግዚአብሔርም የመስዋዕቱን መአዛ አሸተተ። ዳግመኛም የሰውን ልጅ ላያጠፋ ቃል ገባ።ዘፍ 8፡21 ይህ ምሳሌ ነው።እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር አዲስና ዘላለማዊ ቃል የገባው ልጁ ኢየሱስ ራሱን መስዋዕት አድርጎ ያቀረበውን መልካም መአዛ ያለውን ቤዛነቱን አሽትቶ ነው።
” ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ “ኤፌ 5፡2

እኛ እግዚአብሔር ፊት የሚያቀርብ መአዛ የለንም።ሰው ኢየሱስ ከሌለው በእግዚአብሔር ፊት ይዞት የሚቀርበው የራሱን ጠረን ነው።የሰው ጠረን ደግሞ ሐጢያትና ሞት ስለሆነ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት የለውም።ጌታ ኢየሱስን ስንቀበል ግን እግዚአብሔር የተቀበለው መልካሙ መአዛ በውስጣችን ኖረ።አሁን በእግዚአብሔር ፊት ምን ይዤ ልቅረብ ብለን አንጨነቅም።አብ ደስ ብሎት የሚያሸተው በቅድስና የተዋበውን ቤዛችን ኢየሱስን ይዘን ወደ ሰማይ መቅደስ እንገባለን።አስታውሱ!እግዚአብሔር ወደኛ በምህረት የሚመጣው ድካም ስለሌለብን ሳይሆን በእኛ ላይ ያለው የልጁ የኢየሱስ ጠረን ስለሚስበው ነው።
የሐጢያትና የሞት ጠረናችን በኢየሱስ ተወግዶላናል።

በጎ መአዛችን ኢየሱስ ስሙ ይባረክ።
349 views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-24 22:49:27 ስለ እውነት ብቻ እኖራለሁና እንዲህ ብዬ እመሰክራለው።

"የኢየሱስ ደም ብቻ አስታራቂ ነው"!

በብሉይ ኪዳን አንድ ሰው ሐጥያት ከሰራና ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ ከወደደ የበግ ጠቦት ይዞ ወደ ካህን ዘንድ ይሄዳል።ካህኑም በጉን ስለ ሐጥያተኛው መስዋዕት አድርጎ ያቀርባል።የሐጥያት ቅጣት የሆነውን ሞት በጉ
ተቀብሏልና ሐጥያተኛው ይቅርታ ያገኛል።ዘሌ 16፡6

ይህ ምሳሌነቱ ለአዲስ ኪዳን ነው።ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ላይ ሲሞት የእያንዳንዳችንን ሐጥያት ተሸክሞ
ነበር።”እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ”።ኢሳ 53፡6 አሁን ከእግዚአብሔር ጋር የምንታረቅበት ብዙ መንገድ ሳይሆን አንድ መንገድ አለ።እርሱም ከ 2000 አመት በፊት ስለእኛ የፈሰሰው የመሲሁ ደም።ከዚህ ደም ውጪ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር ማስታረቅ የሚችል አካል የለም።ቢኖርማ ኢየሱስ ክርስቶስ ያን ሁሉ መከራ መቀበል ባላስፈለገው ነበር።በብሉይ ኪዳን ከበጉ ደም ውጪ ዕርቅ እንደሌለ በአዲስ ኪዳንም ከጌታ ደም ውጪ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ አይቻልም።ደምም ሳይፈስ ስርየት የለም።ዕብ 9:22

ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ከራሱ፣ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አስታርቆናል ብለን ካመንን አሁንም በደሙ
ያስታርቀናል ብለን ለማመን ልንቸገር አይገባም።ደሙ ለዘላለም ህያው ስለሆነ ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር
የማስታረቅ አቅም አለው። ዛሬም ደክመን ሐጥያትን ብናደርግ ወደ እግዚአብሔር መግቢያችንና አስታራቂያችን ደሙ ነው። "እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው" ሮሜ 3፡25 ቅዱስ ጳውሎስ የሚለን ደሙ ማስተስሪያ ነው።ደሙ የሚገኘው ደግሞ በዕምነት ነው።ሐጢአተኛ ስለሱ በፈሰሰው ደም አምኖ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር ጋር ይታረቃል።እግዚብሔር የሐጥያት ማስተስሪያ አድርጎ ደሙን ካቆመው እኛ ለምን
የራሳችንን ማስተስሪያ መንገድ ለማቆም እንፈልጋለን ?እግዚአብሔር ይቅር የሚለን ስለፈሰሰው ስለ ልጁ ደም
ሲል ብቻ ነው።

የመሲሑ ደም ዛሬም ላመኑት ማራቸው እያለ ይጮሃል።
751 views19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 09:53:22 መላዕክትና የኢየሱስ ስም
ቅዱሳን መላዕክት ሊቆጠሩ የማይችሉ ብዙ ደግሞም እያንዳንዳቸው የእግዚአብሔር ክብርና ጸጋ ያለባቸው ሐያላን ናቸው።ይሁን እንጂ ከእነዚህ ሁሉ መላዕክት ኢየሱስ የሚለው ስም ይበልጣል!“ከመላእክት ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ስምን በወረሰ መጠን እንዲሁ ከእነርሱ አብዝቶ ይበልጣል”። ዕብ 1፡4 ስሙ እንዴት ነው ከመላዕክት የሚበልጠው?

ሁሉም መላዕክት በሐጥያቱ ምክንያት ለሞተው ሰው ሕይወትን መስጠትን አልቻሉም።በኢየሱስ ስም ግን ሰው ሕይወትን ያገኛል።”ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።ዮሐ 20፡31

ሁሉም መልዕክት በአንድ ላይ ሆነው የሰውን ሐጥያት ማስተስረይ አልቻሉም።በስሙ ግን የሐጥያት ይቅርታ ተገኝቷል።”በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል።”ሐዋ 10፡43

መላዕክት በሐጥያቱ ምክንያት ባሪያ የሆነውን ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ሊያደርጉት አልቻሉም።ኢየሱስ በሚለው ስም በኩል ግን ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ሊሆን ይችላል።”ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤”ዮሐ 1፡12

መላዕክት ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጸሎቱ እንዲሰማ ማድረግ አይችሉም።በስሙ ግን ጸሎት ተቀባይነት ያገኛል።ኢየሱስ እንዲህ አለ”አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል።”ዮሐ 16፡23 አብ ያለ ልክ ከፍ ከፍ ያደረገው ስግደትም የተገባው ራሱን ዝቅ ላደረገው ለጌታ ስም ነው።"በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥"ፊሊ 2:8

ከእርሱ ውጪ መዳኛ ስም የለም።ሐዋ 4:12 ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤ዕብ 3፡1

በስሙ አትፈሩ።ዝማሬ ኢየሱስ ለሚለው ስም ይሁን።
458 views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-19 22:04:56 የታረደው በግ
ከሰማይ የወረደው በሸላቾቹ ፊት ዝም ያለው ያለ ልክ የተዋረደው የእግዚአብሔር በግ ሐጥያት የሌለበት ንጹህ ነው።በጉ የታረደው የአለምን ሁሉ ሐጥያት በመሸከሙ ነው።በመታረዱ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን የጸብ ግድግዳ አፍርሷል።ቢታረድም ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷልና በሰማይ ቆሞ ላመኑበት ይማልዳል።ያፈሰሰውሐዋ 7:56

ያፈሰሰው ደሙ ከዘር ሲወርድ ሲዋረድ የመጣን እርግማንን ይሰብራል።ከሰይጣን እስራት ነጻ ያወጣል።ከሞት ያስመልጣል።የታረደው በግ ለተቀበሉት የሚያሳርፍ የህይወት ምግብ ነው።

ዝማሬና ስግደት ለታረደው በግ ኢየሱስ ብቻ ይሁን።
373 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-18 23:54:03 የሐጥያት ይቅርታ
ሰው ሐጥያትን ሰርቶ ወደ እግዚአብሔር መመለስን ቢወድ ሐጥያቱ የሚሰረይበትና ይቅርታ የሚያገኝበት መንገዱ የኢየሱስ ደም ነው።የሰው ጥረት የፍጡር ምልጃ ሐጥያትን ማስተስረይ አይችልም።ይቅርታ ማሰጠት የሚችለው ደሙ ብቻ ነው።"እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው"ሮሜ 3:25 ደሙ ቆሞ ሌላ ይቅርታ ማግኛ መንገድ አንፈልግ።ደሙ የሚገኘው የትም ሳይሆን በዕምነት ነው። ካመነው ሐጥያትን ያስተሰርያል።ሌላ ሐጥያት የሚሰረይበት መንገድ ቢኖር ኢየሱስ ለምን ሞተ?ቃሉ እንዲህ ይላል "በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት ነው"።ኤፌ 1:7

ሐጥያታችንን ለማስተስረይ ደሙ ብቻውን በቂ ነው።
372 views20:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-10 20:44:37 የውጤታማ ጸሎት ምስጢር
ጸሎት የማይደረገው እንዲደረግ የማይሆነው እንዲሆን የማድረግ አቅም አለው።ጸሎት በነገራችን ላይ እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባ የምንጋብዝበት ነው።ጸሎት የአምልኮ አንዱ መገለጫ ነው።ስለዚህ ሁሌም ቢሆን መጸለይ ያለብን በሁሉ ቦታ ወደሚገኘው ሁሉን ማድረግ ወደሚችለውና ሁሉን ወደሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ሊሆን ይገባል።ጌታችን ኢየሱስ ጸሎትን ባስተማረበት ክፍል ላይ የጸሎታችን አድራሻ አባታችን እግዚአብሔር ብቻ እንዲሆን ነው የነገረን።”ስትጸልዩ እንዲህ በሉ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ”ሉቃ 11፡2 እግዚአብሔር ብቻውን ጸሎታችንንን ለመስማት በቂ ነውና ወደ ፍጡር ልንጸልይ አይገባም።

እኔ ሐጢአተኛ ነኝ።ጸሎቴን ወደ ቅዱሱ እግዚአብሔር የሚያደርስ ያስፈልገኛል እንል ይሆናል።ጌታችን ኢየሱስ እኔ የሞትኩት አይደለም ጸሎታችሁን እንናንተን ራሱ ወደ አብ ለማስገባት ነውና ማንም አያስፈልጋችሁም ይለናል። ኤፌ 2፡18 ጸሎታችን የሚያርገው በጌታ ኢየሱስ ስም ስንጸልይ ነው።ምንም ደካሞች ብንሆን በሰማይ ከሚታወቀው ኢየሱስ ከሚለው ስም የተነሳ እንሰማለን።”አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል።”ዮሐ 16፡23 እስካሁን ድረስ በስሙ መጸለይን ላልተለማመድን ጌታ እንዲህ ይላል”እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፤ ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ።”ዮሐ 16፡24 በኢየሱስ ሞት የታረቀን አባትችን ይወደናል ይሰማናል።ስለዚህ ከእርሱ ውጪ ወደ ማንም አንጸልይ።የጌታ ኢየሱስ ስም የጸሎታችን ጉልበት ነው።በስሙ አምነን ዘወትር እንጸልይ።

ድካማችን ሳያይ በጌታ ኢየሱስ ምክንያት ለሚሰማን አብ ክብር ይሁንለት።
463 views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-09 09:26:16 አማላጃችን
በዳይ ተበዳይን ከበደሉ ክብደት የተነሳ ለማየት ሲቸገር አማልጅ ይልካል።በእኛና በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንዲህ አልሆነም።ከበደላችን የተነሳ እኛን ወክሎ የሚያስታርቀንና የምንለከው አማላጅ ፍጡር አላገኘንም ነበር።ተበዳይ የሆነው እግዚአብሔር ራሱ ከወደደን ትልቅ ፍቅሩ የተነሳ ራሱ ልጁን አማልጅ አድርጎ ላከልን።ልጁ ጌታ ኢየሱስ ስለ ሐጢአታችን በመሞት ደሙን ቤዛ አድርጎ በመክፈል አማላደን።“እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”ኢሳ 53፡12

የኢየሱስ የምልጃ አገልግሎት ዛሬ ላይ ያበቃ ሳይሆን ዛሬም አሁንም ህያው ሆኖ ላመኑት የሚሰራ ነው።ቃሉ እንዲህ ይላል”እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል”ዕብ 7፡24 በሰማይ ብዙ ቅዱሳን አሉ።በእኛ ጉዳይ የተሾመና ስለ እኛ የሚማልድልን ግን ጌታ ኢየሱስ ብቻ ነው። ስለ እኛ ቤዛ ከሆነ በኋላ ደሙን ይዞ ወደ ሰማይ መቅደስ የሄደው ለዚሁ አገልግሎት ነው።”ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ”።ዕብ 9፡24

ኢየሱስ እኛን ያማለደን ደሙን ካሳ አድርጎ ከፍሎ ነው።ማማለድ የእርሱ አገልግሎት ብቻ ነው።ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ በደም የተፈጸመው የእርሱ የምልጃ አገልግሎት ብቻውን በቂ ነው።”የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው”።ሮሜ 8፡34

ለሐጢአተኛው ለማለደ ለኢየሱስ ክብር ይሁንለት።
447 views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ