Get Mystery Box with random crypto!

ጵራቅሊጦስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ peraclete — ጵራቅሊጦስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ peraclete — ጵራቅሊጦስ
የሰርጥ አድራሻ: @peraclete
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 577
የሰርጥ መግለጫ

“እግዚአብሔር ይላል፦ በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ”
— ሐዋርያት 2፥17

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-15 21:49:36 የእግዚአብሔርን ቃል የሚጠሙ ሰዎች Subscribe የሚያደርጉት ቻናል


182 views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 22:48:39
366 views19:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 22:47:31 ኢየሱስ አለልን!
ሐጢአተኛ ነኝ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ አልችልም አንበል።ኢየሱስ ወደ አብ የምንገባበት ድፍረታችን ነው።በእግዚአብሔር ፊት ይዤ የምቀርበው ነገር የለኝም አንበል።አብ የረካበት መስዋዕት የሆነልን ኢየሱስ አለልን።ምን ለብሼ እግዚአብሔር ፊት ልቅረብ አንበል።ኢየሱስ ጉድፍ የሌለበት ልብሳችን ነው።ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ መልካም ጠረን የለኝም አንበል።ኢየሱስ በአብ ፊት መአዛችን ነው።ኢየሱስ በድካማችን ሐይሉን፣በሐጢአታችን ምህረቱን ገልጧል።በባዶነታችን ላይ እሱ ሙላታችን ነው።

አለኝ ብዬ የምመካብህ ኢየሱስ ተባረክ።
395 views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 13:59:22
የጌታችን ሕማም በተለየ መልኩ በሚታሰብበት በዚህ ሰሞን"ኪዳነ ምህረት ማነው"በሚል ርዕስ ኤርሚያስና ሜሎስ ይወያያሉ።

ዛሬ ሰኞ 9/8/2014 ማታ 2:30 በቲክቶክ በዚህ ሊንክ እንገናኝ።
tiktok.com/@ermiaskiros
ስለ እውነት ብቻ የምንኖርበትን ዘመን የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን።

https://vm.tiktok.com/ZM8Tdg3eC/
365 views10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-14 22:32:54 ይሄ ነው የገባኝ......
ውበት ይረግፋል።ዝነኝነትም ይጠፋል።ገንዘብም ያልቃል።ሀይልም ይደክማል።ስልጣንም ይሻራል።ወዳጅም ይሸሻል።ምንም ነገር ባለበት አለመቆየት የምድር ህግ ነው።ምን የሚያስመካ ነገር አለ?

የህይወት ዋስትና በኢየሱስ አምኖ ከእግዚአብሔር መኖር ብቻ ነው።
348 views19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 22:24:02 ታቦት(ክፍል 2)
በብሉይ ኪዳን መቅደሱ የእግዚአብሔር ቤት የሚሆነው ከታቦቱ የተነሳ ነበር።በአዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር በመካከላችን የሚኖረው ታቦት ስለያዝን ሳይሆን በስሙ ስለተሰበሰብን ነው።ጌታ እንዲህ ብሎ ቃል ገብቶልናል
" ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና" ማቴ 18:20

ስሙ ከታቦት ይበልጣል።ኢየሱስ የሚለው ስም ብቻውን በቂ ነው።
437 views19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-04 22:14:24 ታቦት
እግዚአብሔር አንድያ ልጁን መስዋዕት አድርጎ ያቀረበው ከእኛ ጋር ለመሆን ነው።እግዚአብሔር በአዲስ ኪዳን ከእኛ ጋር የሆነውና አማኑኤል የተባለው በኢየሱስ በኩል እንጂ በታቦት በኩል አይደለም።ስለዚህ በአዲስ ኪዳን የእግዚአብሔር ማደሪያው የሰው ልብ እንጂ የሰው እጅ የሰራው ታቦት አይደለም።" የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?"1ቆሮ 3:16

ኢየሱስ በደሙ ያጠበን ሊኖርብን ነው።ታቦቱን(ማደሪያውን)የሰው ልጅ ላደረገ ምስጋና ይሁንለት።
435 views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-03 00:09:38 እግዚአብሔር እንዲህ አስተማረኝ...
ዛሬ እረፍቴ ስለነበር በማለዳ ራሴን በዋና ለማነቃቃት ወደ አንድ ቦታ ሄድኩ።አንድ አባት ትንሽ ልጁን ውሐ ውስጥ ይዞ ዋና ሊያስለምደው ይሞክራል።ጥልቀት ወዳለበት ቦታ እየቀረቡ ሲሄዱ ልጁ በፍርሀት ውስጥ ሆኖ እያለቀሰ ካልወጣሁ ማለት ጀመረ።ያኔ አባቱ እንዲህ ሲለው ሰማሁ"አይዞህ አለቅህም"!

ልጁ የያዘውን እጅ ሳይሆን የውሀውን ስምጠት ባየ ጊዜ ፈራ።የእኛም ህይወት እንዲህ ነው።የእግዚአብሔር እጅን ሳይሆን ሁኔታዎቻችንን ስናይ እንጨነቃለን።እግዚአብሔር ግን በማንኛውም ከባድ በሚመስል ህይወት ውስጥ እንድናልፍ የሚፈቅደው በያዘን እጁ ስለሚተማመን ነው።ወዳጆቼ አትፍሩ አትጨነቁ።አንጠፋም ደግሞም አንወድቅም።ምክንያቱም እርሱ እንዲህ ብሎናል"አልለቅህም ከቶም አልተውህም"ዕብ 13:5

ጌታዬ ኢየሱስ ስለ እኔ የቆሰለው እጅህ ይዞኛልና አመሰግንሀለው።ይሄ እጅ እንደ ሰው ይዞ የማይለቅ መሆኑን አስተውል ዘንድ በየቀኑ አይኔን ክፈት።
789 views21:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-26 21:03:17
466 views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-23 22:40:29 ጠበቃችን ኢየሱስ ነው!
ሐጢአት ሰርተን በሞት እስር ቤት ነበርን።ከኢየሱስ በቀር በዚህ እስር ቤት ያልነበረ ማን አለ?ሮሜ 3:23ጌታ ኢየሱስ ፍጹም ሰው ሆኖ ስለ ሐጢአታችን ደሙን ከፍሎ በሞቱ ማልዶ ነጻ አወጣን።ዛሬም ብንደክም ለሐጥያታችን ይቅርታ እንድናገኝ ሞቼላቸዋለው ብሎ የሚከራከርልን ኢየሱስ ነው።ቃሉ እንዲህ ይላል"ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"1 ዮሐ 2:1

በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም አቅም ስናጣ እሱ ስለ እኛ ይቆምልናል።በደከምን ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት የሚታይልን ያመንነው ኢየሱስ ነው።አብ እስከ ሞት የታዘዘውንና ደስ የተሰኘበትን ጻድቅ ልጁን በልባችን ውስጥ ሲያይ ይራራልናል።

በሰማይ የነበረው ከሳሻችን ሰይጣን ወድቆ ጠበቃችን ቆሟል።ጠበቃ አንተ ስትፈቅድ ነው የሚቆምልህ።የኢየሱስም ጥብቅና በጠበቃነቱ ላመኑበት ብቻ ነው።

የማታሳፍረን ጠበቃችን ኢየሱስ ስምህ በትውልድ መካከል ይክበር።
478 views19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ