Get Mystery Box with random crypto!

Neway Challenge Academy-Official Account

የቴሌግራም ቻናል አርማ newaychallenge — Neway Challenge Academy-Official Account N
የቴሌግራም ቻናል አርማ newaychallenge — Neway Challenge Academy-Official Account
የሰርጥ አድራሻ: @newaychallenge
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.37K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-05-16 15:34:02
እንኳን ደስ አላችሁ!
እንኳን ደስ አለን!
በንፋስ ስልክ ላ/ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት ከ ግንቦት 05-06/2014 ዓ.ም በሁሉም የመንግስትና የግል ት/ቤቶች ተሳታፊነት የትምህርት ፈስቲቫል ተዘጋጅቶ ነበር ። በዚህ ዝግጅት ከ1ኛ-12ኛ የክፍል ደረጃ ያሉ ተማሪዎች የተሳተፉበት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር የተከናወነ ሲሆን በውድድሩ ላይም የነዋይ ቻሌንጅ አካዳሚ 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በአይሲቲ ፣በባዮሎጂ፣ በኬምስትሪ እና በፊዚክስ የፈጠራ ውድድሮች ብርቱ ፉክክር አድርገው በማሸነፋቸው በአጠቃላይ ድምር ውጤት በክ/ከተማው ካሉ የግል እና የመንግስት ት/ቤቶች ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ዋንጫ እና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ወላጀች እና አጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ ለተገኘው ውጤት እንኳን ደስ አለን!
እንኳን ደስ አላችሁ!
ትምህርት ቤቱ!
6.7K views12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 11:06:51 ነዋይ ቻሌንጅ አካዳሚ አ.ማ
22/08/2014 ዓ.ም
የተከበራችሁ ወላጆች
በት/ቤታችን ህገ-ደንብ መሠረት ተማሪዎች በሠዓታቸው ት/ቤት መገኘት፤ የተሟላ እና በስነ ስርዓት የተሠፋ የት/ቤት የደንብ ልብስ መልበስ፤ የተስተካከለ የፀጉር አቆራረጥ እና አሠራርን መተግበር፤ የተሟላ የት/መሣሪያ ይዞ መገኘት እና የመሣሠሉትን የተማሪ ግዴታዎችን ልጅዎ እንዲወጣ/እንድትወጣ በየእለቱ እንዲከታተሉ እናሳስባለን።
እባክዎን የሚከተሉትን መጪ ክንውኖች አንብበው ለተግባራዊነቱ ከልጅዎ ጋር ይስሩ፡፡
1ኛ- በመጪው የኢድ አል ፈጥር በዓል ቀን እና በማግስቱ (በቀጣዩ ቀን) ት/ቤት ዝግ ነው።
2ኛ- ሀሙስ፣ ሚያዝያ 27/2014 ዓ.ም፡- የኢትዮዽያ አርበኞች የድል ቀን (ት/ቤት ዝግ ነው።)
ማሣሠቢያ፡- ከተጠቀሡት ቀናት ዉጪ ከት/ቤት መቅረት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።
ከሠላምታ ጋር!
የት/ቤቱ አስተዳደር
8.0K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-21 10:52:37 ቀን፡- 11/08/2014 ዓ.ም
የተከበራችሁ ወላጆች፤
በያዝነው የሁለተኛ መንፈቅ አመት ት/ቤታችን ከእናንተ ወላጆች እና ተማሪዎቻችን ጋር የበለጠ ተጣምሮ በመስራት በርካታ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ ተማሪዎቻችን የመንፈቀ-ዓመቱን የመጀመሪያ ፈተና ያጠናቀቁ ሲሆን በቀጣይ ለሚመጡ ፈተናዎች / ሞዴል ለ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል/ የበለጠ ተጠናክረው እንዲሰሩ የእናንተ ክትትል እና ድጋፍ በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ልጅዎን ከትምህርቱ በተጨማሪ በስነ-ምግባር ብቁ ለማድረግ ከት/ቤቱ ጋር ተቀራርቦ መስራት አስፈለጊ ነው፡፡ ምንም አይነት ጉዳይ ወይም ቅሬታ ካልዎት ከእኛ ጋር ቀርበው እንዲወያዩ ሁሌም ፍላጎታችን ነው፡፡
የሚያዚያ ወር የባህሪ ማረቂያ መርህ “ማምረት” ሲሆን ይህ መርህ ተማሪዎች አዳዲስ ነገሮችን የማምረት፣የመፈልሰፍ ወይም የመስራት አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ያስተምራል፡፡ ይህን አስፈላጊ የባህሪ ማረቂያ መርህ መሰረት በማድረግ ከልጅዎ ጋር በቤት ውስጥ የበለጠ ይወያዩበት፡፡
እባክዎን የሚከተሉትን ወጪ ክንውኖች አንበብው ለተግባራዊነቱ ከልጅዎ ጋር ይስሩ፡፡
ሀሙስ ሚያዚያ 13/2014 ዓ.ም፡- ትምህርት ለግማሽ ቀን እስከ 6:30 ብቻ ይሆናል፡፡
ከአርብ እስከ ሰኞ፤ ከሚያዚያ 14-17/2014 ዓ.ም፡- የስቅለት በዓል እና የፋሲካ በዓል (ት/ቤት ዝግ ነው)
ስለሆነም ወላጆች ከላይ የተጠቀሱትን ቀናት ክንውኖች ተረድታችሁ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ለልጆቻችሁ እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!
9.2K viewsedited  07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-16 09:59:03 የተከበራችሁ ወላጆች እና ተማሪዎቻችን
እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን!
ነዋይ ቻሌንጅ አካዳሚ እንደተለመደው አሰራሩን አጠንክሮ የቀጠለ ሲሆን በት/ቤታችን እና ተማሪዎቻችን በምናደርገው የተለያዩ ውድድሮች በአኩሪ ውጤት አጠናቅቀናል፡፡
ለምሣሌ ያህልም
የአፀደ ህፃናት ት/ቤቶቻችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ስምንት መቶ በሚያህሉ ት/ቤቶች ላይ ምዘና አካሒዶ የአፀደ ህፃናት ት/ቤታችን ከአምስቱ የተመረጡ ት/ቤቶች አንዱ ሲሆን የአንደኛ ደረጃ ት/ቤታችን (ከ1ኛ-8ኛ) ደግሞ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ 2ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
በተጨማሪም የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት በክ/ከተማው ያሉትን አጠቃላይ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች ያሳተፈ የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር አካሂዷል፡፡ በዚህም ተማሪዎቻችን በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ተወዳድረው በሁለቱም 2ኛ ደረጃ በመውጣት አሸንፈዋል፡፡ ት/ቤታችንም ከአጠቃላይ 2ኛ ደረጃን በመያዝ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ለተመዘገበው ውጤት የመላው የት/ቤቱ ማህበረሰብ ጥረት ነው፡፡ በቀጣይም ያሉ እንከኖችን እያፀዳን አብረን እንሰራለን፡፡
ከልብ እናመሰግናለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር
8.8K views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-14 14:41:15 ለነዋይ ቻሌንጅ ትምህርት ቤት የተማሪ ሰርቪስ ተጠቃሚዎች በሙሉ
አውራሪስ ግስላ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር የትራንስፖርት አገልግሎቱን በተቀላጠፈ ሁኔታ ለመስጠት ወላጆች በአቅራቢያቸው በሚገኘውን የአዋሽ ባንክ የአገልግሎት ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያደርግ አሰራር ቢቀይስም አንዳንድ ወላጆች በረዳት ሹፌሮች በኩል ለአገልግሎት ክፍያ ጥሬ ገንዘብ እየላኩ ይገኛሉ። በዚህም ምክኒያት ጥቂት ረዳቶች ለግዜው በቁጥር ያልታወቀ ገንዘብ በመያዝ ከስራ ገበታቸው ጠፍተዋል። ይህ ሁኔታ በድጋሚ እንዳይፈጠር ወላጆች በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ (አካውንት ቁጥር 01320142195500 ሰለሞን ተፈራ ወልደጻዲቅ ) በመሄድ ክፍያቸውን እንዲፈጽሙ አደራ እንላለን።
አውራሪስ ግስላ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር
7.4K views11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ