Get Mystery Box with random crypto!

የክርስትንና መንገድ እንደ 'አስቸጋሪ፣ የማይቻልና ጠባብ' አድርገን እንደናስብ የሚያደርገን፣ ለሥጋ | ናዝራዊ Tube

የክርስትንና መንገድ እንደ "አስቸጋሪ፣ የማይቻልና ጠባብ" አድርገን እንደናስብ የሚያደርገን፣ ለሥጋችን የሚመቸውን ሰፊውን መንገድ ስለምንመረጥ ነው። ከክርስቶስ ፍቅር ይልቅ በሰፊው በር በኩል የምናገኘው የኀጢአት ደስታ ስለሚበልጥብን ነው። ስለ በደላችንና ስለኀጢአታችን በመስቅል ሞት ሕይወቱን ስለ ለእኛ አሳልፎ የሰጠው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "አስጨናቂ ገዢ" አይደለም።

በመስቀሉ ላይ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፍቅር የተረዳ ሰው ጠባቡን መንገድ እንደ ዕዳ አያየውም። ይልቁንም ለዓለምና ለሥጋው ፈቃድ በየጊዜው ይሞቷል። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚለው፣ “ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። አሁንም በሥጋ የምኖረው ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን አሳልፎ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለኝ እምነት ነው።” ( ገላትያ 2 : 20) ክርስቶስን መሲሕ ብቻ ሳይሆን ጌታ አድርጐ በልቡ ላይ አንግሧል።  ከኀጢአት ከሚገኘው ደስታ ይልቅ በማይወዳድር መልኩ በክርስቶስ ፍቅርና ክብር ደስ ይለዋል። የዓለም ሳይሆን የክርስቶስ ፍቅር እስረኛ በመሆኑ በጠባቡ በር ይገባል። ጠባቡ በር የፍቅርና የክብር በር ነው። በአንድ ጊዜ የጌታም የዓለምና የሥጋ መሆን አይቻልም። የት ይሆን ያለነው?

አቤቱ፤ የመስቀልህ ፍቅር ያድሰን። አሜን!

ግርማ በቀለ (ዶ/ር)
@nazrawi_tube