Get Mystery Box with random crypto!

'መንፈስን አታዳፍኑ' *** ከጠፊው ዓለም የተጠሩት የእግዚአብሔር ኅሩያን (ምርጦች) የእምነት ተ | ናዝራዊ Tube

"መንፈስን አታዳፍኑ"
***
ከጠፊው ዓለም የተጠሩት የእግዚአብሔር ኅሩያን (ምርጦች) የእምነት ተጓዦች ናቸው። አዎ አማኞች ወደ ቤታችን በመኼድ ላይ ያለን የእምነት ተጓዦች ነን። ወደ ዘላለም ቤታችን በመኼድ ላይ ነን። ቲም ፌሎስ አንድ አገላለጽ አለው፤ “ዘላን ቤት የለውም፤ ሽፍታ ከቤቱ የሸሸ ነው፤ እንግዳ ከቤቱ የራቀ ሲኾን፥ የእምነት ተጓዥ ግን ወደ ቤቱ የሚኼድ ነው።” አዎ፥ ተጓዦች ነን።


.
በእምነት በምንጓዝበት ጊዜ ታዲያ ብቻችንን አይደለንም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው። የዚህ ዐብሮነቱ ማረጋገጫው ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ማደሩ ነው። አዎ፥ ጌታ እንደ ተስፋ ቃሉ “ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንኾን፥ በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው” (ቲቶ 3፥6-7)። ...
.
ከማንኛውም ክፉ ትምህርትና ተመክሮ ለመራቅ መፍትሔው እውነተኛውን አሠራር ማዳፈን አለመኾኑን መረዳት የተገባ ነው (1ቆሮ. 14፥39-40)። በመንፈስ ነጻነትና በድንጋጌ ሥርዐት መካከል ተገቢ ሚዛን መጠበቅ ያስፈልጋል። ትእዛዙም “መንፈስን አታጥፉ፤ ትንቢትን አትናቁ፤ ኹሉን ፈትኑ፤ መልካሙንም ያዙ፤ ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ” (1ተሰ. 5፥20) የሚል ነውና። ..
.
... ሙሉውን መልእክት ለማግኘት፦