ፍቅረ ቢጽ ከ ፍቅረ እግዚአብሔር የሚያደርሰው ነው።(አረጋዊ መንፈሳዊ)
ክርስቲያን ወንድምህን በፍቅር ባየሀው ጊዜ እግዚአብሔር ማየትህ ነው።(ቀሌሜንጦስ)
ባልንጀሮችህ አንድ ሺ ሊሆኑ ይችላሉ ፣ ያንተን ምሥጢር ደብቆ የሚይዘው ግን አንድ ነው።(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ )
ከላይህ ያለ ሰው አስተማሪ የሚሆነው በ እውቀቱ ከሆነ ሊቅ ልትሆን ትችላለህ በ ህይወቱ ከሆነ ግን ክርስትያን ትሆናለህ።(አቡነ ሺኖዳ)
የትህትና ከፍታ እጅግ ታላቅ ነው፤የመታበይ ጥልቀት ደግሞ እጅግ ጥልቅ ነው። የመጀመርያውን እንድትከተል ወደዚህኛው ደግሞ እንዳትወድቅ እመክራለሁ።(አባ ኤስድሮስ)
በሌሎች ላይ መፍረድ የ አንድ ሰው የ ትዕቢት ውጤት ነው፤ ትሑት ሰው ግን ሁሉ ሰው ያከብራል፤ከ እርሱ የተሻሉ እንደሆኑ ያስባል።(ቅዱስ ዕንባቆም)
ለተቸገረው ሰው በጎ ነገርን ማድረግ አትከልክል ልታደርግለት የሚቻልህ ሲሆን በወዳጅህ አትክፋ።(ቅዱስ ፖሊካርፐስ)
የ እውቀት ደግነቱ ከሁሉ ጋር መስማማትና መግባባት ነው፤የማይቻለውን እሸከማለሁ የሚል ሰው ለመሸከም የሚችለውን ያጣል።(አንጋረ ፍላስፋ)