Get Mystery Box with random crypto!

ምጥን ቅመም (Mitin Kimem)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mitinkimem — ምጥን ቅመም (Mitin Kimem)
የቴሌግራም ቻናል አርማ mitinkimem — ምጥን ቅመም (Mitin Kimem)
የሰርጥ አድራሻ: @mitinkimem
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 1.09K
የሰርጥ መግለጫ

እያሳሳቁ ቁም ነገር የሚያስጨብጡ ጽሁፎችን እናደርሶታለን።
https://t.me/joinchat/AAAAAEW4c6a4s66UQCzegg

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2020-10-09 07:05:08 + ጭንብሎቻችንን የምናወልቀው መቼ ይሆን? +
ጭንብል አድርጎ መዞር ያስጨንቃል አይደል? መቼ ነው ግን የምንገላገለው? ሰው እንዴት ተሸፍኖ ይኖራል!
የኮሮናን መከላከያ ጭንብል ማለቴ አይደለም፡፡ እሱ ትናንት የመጣ ነው፡፡ አብሮን የኖረውንና የሚኖረውን ጭንብል ማለቴ ነው፡፡ ማስመሰል ይባላል፡፡
ያልሆኑትን መሆን ፣ በልብ እየተራገሙ በአፍ መመረቅ ፣ ከጀርባ እያሙ ከፊት ማመስገን እንዴት የሚያስጨንቅ ጭንብል ነው? ከበሽታ የሚከላከል ሳይሆን ራሱ በሽታ የሆነ ጭምብል፡፡
እኔ የምላችሁ ጭንብል ይሁዳ ያደረገውን ‘ለድሆች ሊሠጥ ይገባል’ የሚል የማስመሰል አዛኝነት ጭንብል ነበር፡፡ ለድሃ አሳቢነት በጣም ብዙዎች የሚለብሱት ጭንብል ነው፡፡ ‘ሕዝባችን ተበደለ ተራበ ተጠማ’ እያሉ እነሱ ጠግበው የሚኖሩ የአዛኝ ጭንብል ለባሾች ዓለምን ሞልተዋታል፡፡
ጌታውን ሰላም ላንተ ይሁን ብሎ እየሳመ የሸጠበት ጭንብል ደግሞ ጌታን ያቆሰለ ጭንብል ነበር:: "የታመንኩበት የሰላሜ ሰው እንጀራዬን የበላ ተረከዙን በእኔ ላይ አነሣ" ብሎ ያዘነበት በዚህ ነው::
ሔሮድስ ደግሞ አለልህ፡፡ ‘ሕፃኑ ያለበትን ንገሩኝና መጥቼ ልስገድለት’ እያለ ሊገድል የሚያቅድ ባለ ጭንብል፡፡ ውስጡ በክፋት ተሞልቶ በፍቅር የሚያወራ ስንት ሔሮድስ አለ፡፡
ከፊት ለፊት በፍቅር እያወሩ ሰውዬው ዞር ሲር ‘ስታየው ሰው ይመስላል...’ ብሎ በሐሜት ጀርባውን መንከስ /backbiting እንዲል ፈረንጅ/ ጭንብል ነው፡፡ ከፊት ለፊት ‘ውይ ሲያምርብሽ’ ብሎ በልብ ‘ምን ትመስላለች? አማረብኝ ብላ ነው’ ማለት ጭንብል ነው፡፡ ያልጣፈጠንን ምግብ ‘እጅሽን ይባርከው’ ብለን ስንወጣ ‘አይ ሙያ’ ብሎ ማሽሟጠጥ ጭንብል ነው፡፡ ይኼ ቀለል ያለው ምሳሌ ነው ፤ ሁላችንም ጋር ግን የማስመሰል ምሳሌዎች አሉ፡፡
ይህ የማስመሰል ጭንብል ወደ ሃይማኖትም ዘልቆ ይገባል፡፡ በሰዎች ፊት በጣም መንፈሳዊ ሆኖ መታየት እጅግ ቀላል ነው፡፡ አስመሳይ ክርስቲያን ሆኖ በሰዎች ላይ ክፋት ከሚሠራ ሰው በላይ ሃይማኖት እንዲጠላ የሚያደርግ ሰው የለም፡፡ እንደ ኒቼ ያሉ ፈጣሪ የለም ባዮች ‘እኔ በክርስትና እንዳምን ክርስቲያኖች ድነው ማየት እፈልጋለሁ’’ እስከማለት ያደረሳቸው የማስመሰል ክርስትና ነበር፡፡ ማስመሰልን ፈጣሪ አጥብቆ ይጠላል ፤ ምክንያቱም እርሱ እንደሰው በትወና ችሎታ አይታለልም፡፡ ሳሙኤልን ልኮ ዳዊትን በቀባበት ዕለት ከሚያምሩት ወንድሞቹ ይልቅ ዳዊትን ለምን መረጠ ሲባል ‘ሰው ፊትን ያያል እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል’ ብሎ መልሶ ነበር፡፡ ልቡን አይቶ የመረጠው ዳዊት ለእግዚአብሔር እንደ ልቡ ሆነለት፡፡
የማስመሰል ጭንብል የሚወልቀው በንስሓ ነው፡፡ እግዚአብሔር ፊት ቆሞ በጭንብል መሸፈን የሞከረ ግን መቼም ከጭንብሉ አይላቀቅም፡፡ የማስመሰል ጭንብል ከኮሮና ጭንብል የሚከፋው የኮሮና ጭንብል ብዙ ጊዜ ብታደርገው እንኳን ከመታፈን ያለፈ ክፋት የለውም፡፡ የማስመሰል ጭንብልን ግን ቶሎ ካላወለቅከው አንተ ራስህ ጭንብል ሆነህ ታርፈዋለን፡፡ ይዋሐድህና የጭንብልህ መልክ ያንተ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ፈጣሪን አፍህ ከልብህ ውስጥህ ከውጪህ እንዲመሳሰል አጥብቀህ ጠይቀው፡፡ አለዚያ ክርስቶስ ‘የተለሰኑ መቃብሮች’ እንዳላቸው ፈሪሳውያን ውስጥህ ሙት ይሆንብሃል፡፡
የማስመሰል ጭንብል እንደ ብልጠት የሚታይበት ዓለም ላይ ነን፡፡ ብዙ ሰዎች በውስጣቸው ሌላ እያሰቡ ላይ ላዩን ማስመሰላቸው ፣ በውሸት ፈገግታ ማግጠጣቸው እንደ ሙያ ይደነቃል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ውስጣቸውን ከፍተው ያሳዩ ጭንብል አልባ ሰዎች ይጎዳሉ እንደ ጅል ይቆጠራሉ፡፡
ሆኖም በዕለተ ምጽዓት የሥጋ ለባሽ ሁሉ ሥራው የሚገለጥበት ቀን ብዙ ጭንብሎች ይወልቃሉ፡፡ ጭንብሉ ክፉ መስሎ ውስጡ ንጹሕ የሆነውም ፣ ውስጡ ለሰው ክፋት እያሰበ ጭንብሉን በደግነት የሚቀባባውም ታሪኩ ይወጣል፡፡
በዜና አበው አንድን ታላቅ አባት አንድ ወጣት መነኩሴ እንዲህ ሲል ጠየቃቸው ፦
ወደ ገነት ስንገባ እርስ በእርሳችን እንተዋወቃለን ወይ?
እርሳቸውም መለሱ ፦ ኸረ እንዲያውም ገነት እስክንገባ ድረስ አንተዋወቅም! አሉት፡፡
እውነት ነው ፤ እዚህ ምድር ላይ በጭንብል ታፍነን የምንተዋወቅ ይመስለናል እንጂ አንተዋወቅም፡፡ ትክክለኛው ትውውቅ ያለው ሰው እንደ ሥራው በሚከፈለው ጭንብሉን በመቃብር ጥሎ በሚሔድበት በዚያኛው ዓለም ነው፡፡
‘ክፋት በልቡ ሳለ ፍቅርን የሚናገር ከንፈር በብር ዝገት እንደተለበጠ የሸክላ ዕቃ ነው’ /ምሳ. 26፡23/
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 15 2012 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
4.4K viewsYishak Kelemework, 04:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-06 09:53:11
#ETHIOPIA | ~ ሁላችሁም ስሙት፣ ተመልከቱት፣ ላላየም አሳዩት፣ አሰሙትም። ለልጆቻችሁም አሳዩዋቸው። ይኸው ነው።
ለ 10 ሰው ሼር አርጉት
•••
የዐማራ ልጅ በክልላችን አይወለድም። የክርስቲያን የኦርቶዶክስ ልጅ በክልላችን አይወለድም ብለው የ9 ወር እርጉዟን የደረሰች ነፍሰጡር አሰቃይተው የገደሏት እዚያው ሻሸመኔ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ውስጥ ነው። ከነ ጽንሷ ነው የገደሏት። የቤተ ክርስቲያን ኮሚቴ፣ ንቁ ተሳታፊ በመሆኗ ነው ይሄ መከራ የወረደባት። ባለማዕተብ ስለሆነች ጽንፈኞቹ አላህ ወአክበር ብለው አጠፏት። እናትንም ጽንሱንም አጠፉ። ገደሉ።

ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ይሄ የተኛ ሆዳም የተዋሕዶ ልጅ ይነቃ ዘንድ፣ ራሱን መከላከል ይጀምር ዘንድ፣ መንግሥትም ዓለም አቀፉም ማኅበረሰብ ጉዳዩን አይቶ ፍርድ ባይሰጥ እንኳ ይታዘብ ዘንድ፣ ሚዲያዎች ባይዘግቡትም ትውልዱ ይሄን አረመኔያዊ ግፍ ያየው ይመለከተው ዘንድ በደንብ አሰራጩት። በደንብም አስተላልፉት።

ለ 10 ሰው ሼር አርጉት

እስኪ ምንም ባታረጉ እንኳ ለጓደኞችዎ ና በ ግሩፕ ላይ #SHARE አርጉ ይሄ ያቅትሀል ለቤተክርስቲያን

መልእክቶቻችሁን በ @Christianbrothershood እንድታደርሱን በትሕትና እንጠይቃለን። ኦርቶዶክሳውያንን ወደዚህ ይጋብዙ @Christianbrotherhood
3.3K viewsYishak Kelemework, 06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-07-31 07:17:51 ሁሉም ነገር ለበጎ ነው:
+ የተሠጠህን ቁጠር +

ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው:: የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም:: ዕባብ ደግሞ የስይጣን አንደበት ነበረ::

ሰይጣን እንዲህ አላት :- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት።


ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም:: የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ:: ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ::

ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም:: ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር:: ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቶአት ሔደ:: ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች:: የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች::

ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል። በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን:: ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ:: ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ:: አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ::

ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር::
@Mitinkimem
@Mitinkimem
@Mitinkimem
3.0K viewsYishak Kelemework, 04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-07-30 09:31:13 # ልትረሳኝ_ትችላለህ
# አስተማሪ_ታሪክ
ከአንዲት ጉንዳን ጋር የተደረገ ውይይት ንጉሥ ሰሎሞን ለተፈጥሮ ባለው ፍቅር ይታወቃል እርሱ በየጊዜው በአትክልት ስፍራዎቹ በወንዝ ዳርቻዎችና በተራራዎች ላይ ይዘዋወር ነበር::
እርሱ እንስሳትን ወፎችን ዓሳዎችንና ነፍሳትን በፍላጎት በመመልከትና በደመ ነፍሳቸው ውስጥ የተገለጠውን የጥበባቸውን ጠባይ በማየት እግዚአብሔር ለእነርሱ ያለውን እንክብካቤ ያረጋግጥ ነበር::
ከዕለታት አንድ ቀን ታዲያ ትኩረቱ በአንዲት ትንሽ ጉንዳን ላይ ያርፋል:: ጉንዳኒቱ ከእርሷ ክብደት ብዙ እጥፍ የሚበልጠውን የጥሬ ግማሽ ተሸክማ እየሄደች ነበር:: ጉንዳኗ ይህን የጥሬ ስባሪ ተሸክማ የምትጓዘው በጉድጓዷ ውስጥ ለማከማቸት ነበር።
በዚህ ጊዜ ንጉሡ እጅግ ስለተደነቀ “ይህቺን ጉንዳን ለምንድን ነው የማላስደስታት” ይላል:: እርሱ ይህን ያለው ያላትን ጉልበት ሁሉ በዚህ የጥሬ ድቃቂ ላይ ስታጠፋ ስለተመለከታት ነበር::
“እግዚአብሔር ይህን ያህል ታላቅ ሃብት ለእኔ የሰጠኝ ደስታን ለሕዝቤ ብቻ እንድሰጥ ሳይሆን ለእንስሳት ለወፎችና ለነፍሳት ጭምር እንድሰጥ ነው::”
ንጉሡ ይህን ብሎ ጉንዳኒቱን ካነሳ በኋላ ውስጡ እጅግ ለስላሳ በሆነ ሐር የተነጠፈ የወርቅ ሳጥን ውስጥ ያስቀምጣታል:: ከእርሷ ጋር በወርቅ ሳጥኑ ውስጥ አንድ የስንዴ ቅንጣት ካስቀመጠላት በኋላ ከፈገግታ ጋር በየዕለቱ ምንም ሳትደክሚ የምትበዪውን የስንዴ ቅንጣት ስለምሰጥሽ ከእንግዲህ በኃላ አትደክሚም በጎተራዬ ውስጥ የተትረፈረፈው ጥሬ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን እንስሳትን ወፎችንና ነፍሳትን የሚመግብ ነው አላት:: ንጉሡ እንዲህ ያለውን መልካም እንክብካቤ ለእርሷ ስላደረገላት ጉንዳኒቱ ታመሰግነዋለች::
በሚቀጥለው ቀን ንጉሡ ወደ ጉንዳኒቱ ተመልሶ ሲመጣ የተመገበችውን የአንዱን ቅንጣት ስንዴ ግማሽ እንደሆነ ሲመለከት እጅግ ይደነቃል:: ሌላ አንድ የስንዴ ቅንጣት አስቀምጦላት በሚቀጥለው ቀን ተመልሶ ሲመጣ ጉንዳኗ ግማሹን ቅንጣት ተመግባ ግማሹን እንዳስቀመጠች ይመለከታል::
ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ መሄዱን የተመለከተው ንጉሥ ሰሎሞን ጉንዳኗን ለምንድን ነው ሁል ጊዜ የአንዱን ቅንጣት ስንዴ ግማሽ የምታስቀምጪው? በማለት ይጠይቃታል::
ጉንዳኒቱም እንዲህ በማለት መለሰችለት እኔ በየዕለቱ የስንዴውን ግማሽ የማስቀምጠው ለመጠባበቂያ ነው አንተ ለእኔ ምን ያህል እንክብካቤ እንዳደረግህልኝና በጎተራዎችህ
ውስጥ ምን ያህል የበዛ ጥሬ እንዳለህ አውቃለሁ ይሁን እንጂ አንተ ሰው ስለሆንክ በየዕለቱ የምትከውነው የስራህ ብዛት እኔን እንድትረሳኝ ያደርገሃል ይህ በሚሆንበት ጊዜ ያስቀመጥኳት የስንዴ ቅንጣት ከረሃብ ትታደገኛልች ምግቤን በድካሜ እንዳገኝ የተወኝ እግዚአብሔር አይረሳኝም አንተ ግን ልትረሳኝ ትችላለህ::
በዚህ ጊዜ ንጉሡ ጉንዳኗ ወደ ቀደመ ሕይወቷ ተመልሳ ኑሮዋን እንድትቀጥል ይለቃታል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያልስጠውን ነገር ለእርሷ እንደ ሰጣት ተገንዝቧልና::
# ጭብጥ - ፈጥሮ የማይጥል ወዶ የማይጠላ እግዚአብሔር ብቻ ነው ክርስቲያኖች። ሰው እንደተሰባሪ ብርጭቆ ነው። እግዚአብሔርን የተመረኮዘ አይወድቅም።
@Mitinkimem
@Mitinkimem
@Mitinkimem
2.9K viewsYishak Kelemework, 06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 10:34:25
2.4K viewsYishak Kelemework, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 10:34:25
2.3K viewsYishak Kelemework, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 10:34:25
2.2K viewsYishak Kelemework, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 10:34:25 ክፍል ሠላሳ ስምንት

የአየር_አጋንንት_ፈተና በሱባኤ ወቅት እና በገዳማት

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

አጋንንት በሕይወታችን የሚያደርስብንን ችግር እስክናውቅ እንቸገራለን፣ ውጊያው እስኪገባን ግራ እንጋባለን፣ እውነቱ እስኪገለጥልን እውነቱ ሐሰት ይመስለናል፡፡

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ በክፍል ሠላሳ ሰባት በአጋንንት በመፈተናችን ምን ጥቅም እናገኛለን በሚል ርዕስ ተነጋግረናል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ብዙዎቻችን የምንቸገርበትን እናያለን፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ግን ትንሽ ቅሬታዬን ልናገር፡፡ ሰሞኑን ተከታታይ ትምህርታችን እንደ ቀድሞ በየእለቱ እያቀረብኩላችሁ አይደለም፡፡ ለዚህ ደግሞ ምክንያቴ ሁለት ነበሩ፡፡ አንደኛው የምጽፈው መጽሐፍ ነበር፡፡ ሁለተኛው እንዳያችሁት በቪዲዮ ሁለት ትምህርት ለቅቄ ነበር፡፡ ይህን ለማድረግ ከማንበብ እስከ መዘጋጀት ጊዜ ይፈልጋል፡፡

እንደዛም ሆኖ በተቻለኝ አቅም አቀረብኩት ብዙዎችም ተማሩበት፡፡ አንዳንዶቻችሁ ግን ለምን በቪዲዮ ሆነ፣ በጽሑፍ አድርግልኝ፤ ይህ በዩ ትዩብ የሚለቀቀውን የቪዲዮ ትምህርት ካለብን ሁኔታ አንጻር ማየት አንችልም አላችሁ፡፡ ጥሩ! ግን ሁሌም ትምህርት የሚሰጠው በጽሑፍ ብቻ ነው? እኔስ በጽሑፍ ትምህርት ብቻ ተገድቤ እንድቆም ነው የምትፈልጉት? ደግሞስ በአረብ አገራት በአውሮፓና በአሜሪካ ወዘተ በሥራጰጫና ለማንበብ የማይመቻቸው ግን እየሠሩ የሚያዳምጡ ስንቶች አሉ።

በእርግጥ ይገባኛል አብዛኞቻችሁ የምታውቁኝ በጽሑፍ ትምህርቶቼ ነው ግን ሁሌም እንደዚህ አትጠብቁ፡፡ አንዳንዶች ትምህርት ለምን በቪዲዮ ለቀክ ብለው ቅናት ይሁን ሞኝነት ባላውቅም ለሞራል የምይመጥን ኮሜንት የጻፉትን ብሎክ አድርጊያቸዋለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ጋሽ ማርቆስ የሰጠኝ መብት ስለሆነ ተጠቅሜበታለሁ፡፡ እሺ ጊዜያችንን ላለማባከን ወደ ቀጣይ ትምህርታችን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ወለላይቱ እመቤት ድንግል ማርያም ነገ ሰኔ 21 ቀን በጎልጎታ የሰኔ ጎልጎታ የተሰኘውን ድንቅ የቃል-ኪዳን ጸሎት ጸልያ ለእኛ ለልጆችዋ ቃል-ኪዳን የተቀበችበት ቀን ስለሆነ ነገ የእመቤታችን ወዳጅ እና ልጅ የሆናችሁ በእለተ ቀኗ የሰኔ ጎልጎታን ጸልዩ፡፡ ለምኗት፣ ተማጸኗት፣ ከዚህ ወረርሽኝ በዘርፋፋ ቀሚስሽ በክንፈ ረድኤትሽ ሰውሪኝ፣ ለዓመቱ አድርሺኝ ብላችሁ ጸልዩ፡፡ ይህ በረከት እንዳያልፋችሁ አደራ!

ወዳጆቼ አብዛኞቻችን ወደ ገዳማት ለጸሎት እንሄዳለን፡፡ በሄድንበትም ገዳም ለሰባት፣ ለዐሥራ አራት ቀናት ወይም ለወራት በጸሎት ለማሳለፍ እናቅዳለን፡፡ ገዳም እንደሄድን ከፍተኛ ያለመረጋጋት ክስተት ውስጥ ገብተን ግን ባሰብንበት ሳይሆን ባላሰብንበት ቀን ወደ ቤታችን እንመለሳለን፡፡ በሄድንበት ገዳም መረጋጋት ያቅተናል፣ ሂድ ሂድ የሚል መንፈስ ከውስጣችን ይገፋናል፡፡ ይህ እንግዲህ የአየር አጋንንቱ፣ ውስጣችን ያለው ዓይነ ጥላው፣ ዛሩ፣ ድግምት መተቱ ሰላምና ምቾት ሲያጣ እኛን መስሎ በመገፋፋት ከሄድንበት ገዳም ይመልሰናል፡፡

አንዳንዱን ሊፈወስ፣ ሊቀደስ በሄደበት ገዳም ጊዜውን በወሬና በቧልት እያሳለፈበት፣ ከገዳሙ የጸሎት ሥርዓት እያራቀው ቦታውን ያለማምደውና በዓለም ላይ የተወውን፣ ንስሐ ሊገባበት ያለውን ወይም የገባበትን ኃጢአት እዛው ገዳም ያስፈጽመዋል፡፡ የአየር አጋንንቱ በእንዲህና በሌሎችም አጋንንታዊ ጥበቦች የጀመርናትን ትንሽዋን መንፈሳዊ ሕይወት የርኩሰት እና የከንቱ ሕይወት ያደርግብናል፡፡

ይህ በሚሆንበት ጊዜ እላያችን ላይ ያለው አጋንንት ጾሙን፣ ጸበሉን ጸሎቱን ይለምድና ከነፍስ ከሥጋችን ተዋሕዶ፣ የገዳምን ሕይወት ለምዶ አብሮን ይኖራል፡፡ እኛም ‹‹እዚህ ገዳም ከተቀመጥኩ ሁለት፣ አምስት … ዓመቴ ነው›› እያልን ከመዳን ይልቅ ዓመታት ቆጣሪ፣ ለገዳሙም ሥርዓት አስቸጋሪ ሆነን በመባከን እንኖራለን፡፡ የአየር አጋንንቱ ዓላማችንን በማዘናጋት ድኅነታችንን ያዘገይብናል ያሳልፍብናል፡፡ እኛም አጋንንቱን ገዳሙን ለምደን በከንቱ እንኖራለን፡፡ ቤተሰብ ከዛሬ ነገ ይድናሉ እያሉ በባዶ ተስፋ ይኖራሉ፡፡

ሱባኤውን ብንመለከት ብዙዎቻችን እንዳቅማችን ሱባኤ እንገባለን፡፡ እንደ ፍልሰታ ያለ የሱባኤ ወቅት ሁሉም ለጾም ለጸሎትና ለሱባኤ ይነሳሳል፡፡ ግን አብዛኛው ምዕመን ጾመ ፍልሰታን በሱባኤ አያሳልፍም፡፡ የበረቱትም ዝግ ሱባኤ አልያም አርምሞ ቢይዙም የአየር አጋንንትን ስውር ጥቃት ባለማወቃቸው ሱባኤያቸው ይሰናከላል፡፡ የአየር አጋንቱ በሱባኤ ወቅት ከበድ ብሎ በመምጣት የዘጉ አባቶችን በመፈተንና ፈትኖም ከሱባኤ እስከ ማስወጣት ይደርሳል፡፡ የሚገርመው ማንኛውም ሱባኤ ገብቶ ሳይጨርስ የወጣን ሰው ብትጠይቁ ፈተናው በዝቶባቸው፣ አሟቸው፣ ከሕመማቸው ጽናት የተነሳ መጸለይ አቅቷቸው እንደወጡ አይነግሯችሁም፡፡ የአየር አጋንንቱን የፈተና ገመና ይደብቃሉ፡፡ መልስ እንዳገኙ የሚናገሩም አሉ፡፡

ሱባኤ የገባነው በጸሎት በርትተን ችግራችንን ለማስፈታት ስለሆነ ችግራችን ከእኛው ጋር በእንጥልጥል እንዲቀር የአየር አጋንንቱ ከፍተኛ ፈተና ሊያመጣብን ይችላል፡፡ በተለይ በሱባኤ ውስጥ ቁርጥማት፣ ውጋት፣ የራስ ምታት፣ ብርድ ብርድ የማለት፣ ጽኑ ረሃብና የውሃ ጥማት፣ የማናውቀው ፍርሃት ያመጣብንና እኛም ‹‹ሱባኤ ገብቼ ከምሰቃይ እንደ ሰዉ ሆኜ ብጸልይስ፣ እግዚአብሔር በጊዜው ሊሠራ እኔ ምን ላመጣ ነው›› በማለት በሕሊና ይፈትነናል፡፡ እኛም ይህንን የሐሳብ ጫና መቋቋም ሲያቅተን ለአየር አጋንንት ሐሳብ በመገዛት ከሱባኤ እንወጣለን፡፡

ሱባኤ ገብተው ፈተናውን የተቋቋሙትን ደግሞ ሌሊት በዘንዶ፣ በእባብ፣ በጅብ እና በሌሎችም እየተመሰለ እያስፈራራ ይፈትናቸዋል፡፡ አንዳንዶችን ደግሞ ትዕግሥት በማሳጣት ከሱባኤው ውጣ ውጣ በማለት እረፍትና ሰላም እየነሳቸው ያስወጣቸዋል፡፡ የአየር አጋንንት ሱባኤ ስንገባ የማያባራ የክፋት ሐሳቦችን በውስጣችን እያስገባ፣ በሱባኤያችን ግራ እንድንጋባ ያደርገናል፡፡ በዚህ ስልቱ ያለመረጋጋትን ያጠናውተንና አቋርጠን እንድንወጣ ያደርገናል፡፡

የአየር አጋንንት በሱባኤ ወቅት ድንገተኛ ማዕበል ስለሚሆንብን የሚመጡብንና የሚገጥሙን ፈተናዎች ከእሱ መሆኑን ካወቅን ሱባኤያችንን ልናቋርጥ አይገባም፡፡ በተረፈ ስለ ሱባኤ ሥርዓትና ፈተና ‹‹ከእመቤታችን በሱባኤ መልስ የምናገኝባቸው ጠቃሚ መንገዶች›› የሚለውን መጽሐፌን አንብቡ፡፡

‹‹ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቶአል›› ት.ሆሴ 4÷6

‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ?›› ት.ኢሳ 53÷8

ክፍል ሠላሳ ስምንት

የአየር አጋንንት ክፉ ቂመኛ ያደርጋል

ይቀጥላል ….

ሰኔ 20-10-12 ዓ.ም
አዲስ አበባ
@Mitinkimem
@Mitinkimem
@Mitinkimem
2.3K viewsYishak Kelemework, edited  07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-24 07:49:49 ክፍል ሠላሳ ስድስት

በአጋንንት በመፈተናችን ምን ጥቅም እናገኛለን?

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

አጋንንት በሕይወታችን የሚያደርስብንን ችግር እስክናውቅ እንቸገራለን፣ ውጊያው እስኪገባን ግራ እንጋባለን፣ እውነቱ እስኪገለጥልን እውነቱ ሐሰት ይመስለናል፡፡

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ በክፍል ሠላሳ አምስት በጸሎት የራቀን ዲያቢሎስ በእኛ ስንፍና ወደ እኛ መመለስ አይተናል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ በአጋንንት በመፈተናችን ምን ጥቅም እንደምናገኝ እናያለን፡፡ ወዳጆቼ በአጋንንት በመፈተናችን፣ ሥጋዊ መከራ በመቀበላችን ብዙ መንፈሳዊ ትርፎችን እናገኛለን፡፡ በአጋንንት ተፈትነው ያልወደቁት ቅዱሳን ብዙ ክብር አግኝተዋል፡፡ በአጋንንት ተፈትነው ደግሞ ወድቅው ክብር አጥተዋል፡፡ አጋንንትን ለመዋጋት ስንል አምልኮዋችንን ወደ አንድ ምዕራፍ ከፍ እናደርጋለን፡፡ የአጋንንት ውጊያ የሚበረታብን ከሆነ በጸሎት እንበረታለን፡፡ የአጋንንት ውጊያ የሚበረታብን ከሆነ በጾም እንበረታለን፡፡ የአጋንንት ውጊያ የሚበረታብን ከሆነ በስግደት እንበረታለን፡፡

ከአጋንንትን ውጊያ ለማምለጥ ስንል በመንፈሳዊ ትሩፋታችን ወደ እግዚአብሔር እንጠጋለን፡፡ ወዳጆቼ የአጋንንት ውጊያ ያለበት እና የሌለበት ክርስቲያን እኩል መንፈሳዊ አቋም አይኖራቸውም፡፡ የአጋንንት ውጊያ ያለባቸው ሰዎች በፈተና እንደ ወርቅ የተፈተኑ ስለሆነ ጾም፣ ጸሎት እና ስግደት ለእነሱ ውዴታ ሳይሆን ግዴታ ነው፡፡ ችላ የማይባል ዝንጋኤ የሌለበት ትልቅ ሥራ ነው፡፡ ይህ ትግላቸው ነው ወደ መንፈሳዊ ከፍታ እና ወደ ተሻለ የጸጋ ሕይወት የሚያደርሳቸው፡፡ አባቶቻችን በአጋንንት እጅጉን ስለተፈተኑ ነው ወደ ብቃት ደረጃ የሚደርሱት፡፡

በአጋንንት ተፈትኖ ለነፍሴ ይጠቅመኛል ብሎ በነፍሱ የቆረጠ ነው በጾም በጸሎት በስግደት የሚጠመደው፡፡ ማንም ሳይያዝ የሚለፋ የለም፡፡ የተያዘ ግን ከተያዘበት ችግር ለመውጣት ሲል ብዙ መንፈሳዊ መንገዶችን ሊጓዝ ይችላል፡፡ እነዛ መንገዶች ወደ ጽድቅ ብቻ ሳይሆን ወደ ቅድስና ደረጃ ያደርሱታል፡፡ በፈተናው ትዕግሥት ሊበቃም ይችላል፡፡

ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው›› ይላል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹ፈተና›› ብሎ ጠቅልሎ ነው ያስቀመጠልን፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት ከሥጋ እስከ አጋንንት ያለውን ፈተና ነው የገለጠልን፡፡ ስለዚህ በፈተና መጽናት መባረክም ነው፡፡ እንዲሁም ‹‹የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና›› በማለት በፈተናችን ከጸናን ሰማያዊ ሽልማት እንደሚጠብቀን ይነግረናል፡፡ /ያዕ 1÷12/ ጌታም የሚፈተኑትን ‹‹ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ›› በማለት ነግሮናል፡፡ /ሉቃ 22÷28/

ወዳጆቼ የገጠሙንን ፈተናዎች የምንታገሳቸው፣ በጸሎት ወደ ፈጣሪ የምናመለክትባቸው ከሆነ የፈተና ማዕበላችንን ከመሻገር አልፈን ብዙ መንፈሳዊ ክብር እናገኛለን፡፡ አባቶቻችን ፈተና ሲርቃቸው ጸጋ የራቃቸው ስለሚመስላቸው ፈተናን በጸሎት ለምነው ያመጣሉ፡፡ በመጣባቸው ፈተናም አልፈው ጸጋና ክብር ያገኛሉ፡፡ ለቀደምት አባቶቻችን ፈተና የእግዚአብሔር የፍቅሩ መገለጫ ነበር፡፡ በእኛ ዘንድ ግን እግዚአብሔር እንደተወን፣ እንደረሳን የምንቆጥርበት የተሳሳተ እሳቤያችን ነው፡፡ ስንቶች ከአጋንንት ፈተና ተምረው፣ የደረሰባቸው መከራ ከአጋንንት መሆኑን ተረድተው ጥሩ መንፈሳዊ ሆነዋል፡፡ ስለዚህ አይብዛ እንጂ መፈተናችሁን አትጥሉት፡፡ በመጨረሻ የእግዚአብሔር ክብር፣ ጸጋ ማዳንና ትድግና በእናንተ ላይ ይገለጣልና፡፡

‹‹ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቶአል›› ት.ሆሴ 4÷6

‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ?›› ት.ኢሳ 53÷8

ክፍል ሠላሳ ሰባት

የአየር አጋንንት ክፉ ቂመኛ ያደርጋል

ይቀጥላል ….

ሰኔ 16-10-12 ዓ.ም
አዲስ አበባ
@Mitinkimem
@Mitinkimem
@Mitinkimem
2.1K viewsYishak Kelemework, 04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-21 19:23:47
1.8K viewsYishak Kelemework, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ