2023-02-25 21:05:17
ሁሉም ያልፋል
ይህቺ ምድር ምንም ቋሚ ነገር የላትም።
ያለው ይሄዳል፡ የሄደው ይመጣል።
ፀሐይ ትወጣለች ይነጋል ከዚያ ፀሐይ ትጠልቅና ደግሞ ተመልሶ ይመሻል፡ ድጋሚ ይነጋል አሁንም ተመልሶ ይመሻል ከዚያ ይነጋል ከዚያ…
አዲስ ነው የተባለው ነገር አሮጌ ይሆንና ሌላ አዲስ ነገር ይመጣል…
ፋሽን ታሪክ ይሆንና ሌላ ፋሽን ይመጣል።
ሰላም ይሆናል፡ ወድያው ግን ይበጠበጣል፡ ጦርነት ይነሳል።
ስንወለድ ህፃናት ነበርን፤ ህፃናት እንደሆንን ግን አልቀጥልንም አደግን ወጣት፡ ጎልማሳ ሆንን፤ እንዳደገንም አንቀርም እናረጃለን፤ እንዳረጀንም ደግሞ አንቀጥልም እንሞታለን፣ በነገራችን ላይ ሞተን ብቻ አንቀርም ስማችንም ሳይቀር ይረሳል።
የነበረው ትውልድ አልፎ ይሄ ትውልድ መጣ፡ ይሄም ትውልድ ያልፍና ደግሞ ሌላ ትውልድ ይመጣል።
ትራባለህ ትበላና ትጠግባለህ፤ ተመልሰህ ግን ትራባለህ፤
ዛሬ ብታዝን ሌላ ቀን ትደሰታለህ፤ ግን ሌላ ቀን ደግሞ በሆነ ምክንያት ታዝናለህ፣ ከዚያ ሌላ ቀን ትደሰታለህ፣ ቢሆንም የሆነ ቀን ማዘንህ አይቀርም።
ከዚህ ሁሉ የሚያሳርፍ ጨለማ ማይጨልምበት ሁሌ ብርሃን የሆነበት፣
የማንራብበት የማንጠማበት፣ ምን ልልበስ ሳንል ሰው ያልሰራውን የማያረጅ ነጭ ልብስ ለብሰን የምንደምቅበት፣ ብንሞት ብንራብ ብንጠማ ብለን ማንሰጋበት ዘላለም በሙሉ ደስታ፡ በሙሉ እርካታና ጥጋብ የምንኖርበት፣
አባትህ፣ ወንድምህ፣ ጓደኛህ… ሞቷል፤
እናትህ፣ እህትህ፣ ልጅህ… ሞታለች ለቅሶ ድረስ የማንባልበት በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው ለፀደቁት ቅዱሳን የተዘጋጀ ዘላለማዊ ቤት አለን።
ይችህ የምንኖርባት አለም አሁን አሁን መልሶ ለማስተካከል ወደሚከብድ ውስብስብ ወደሆነ የህይወት ውጥንቅጥ ውስጥ እየገባች እንደሆነ ሁላችንም የምናውቀው ነው፤ አንዱን ሳናስተካክል ሌላው ይበላሻል። ስለዚህ "በዚች ምድር ነገ እንዴት ሆነን እንኖራለን?" ብለን ከመጨነቅ ይልቅ እረፍት የሞላበትን አለም መናፈቅ ይቀላል።
ማራናታ!!!!!!!!
@Missionaries_of_Christ
@Missionaries_of_Christ
182 viewsMiraዥ, 18:05