Get Mystery Box with random crypto!

የማንቂያ ደውል

የቴሌግራም ቻናል አርማ mhretab — የማንቂያ ደውል
የቴሌግራም ቻናል አርማ mhretab — የማንቂያ ደውል
የሰርጥ አድራሻ: @mhretab
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.86K
የሰርጥ መግለጫ

👉 የማንቂያ ደውል በመምህር ምህረታብ አሰፋ የሚቀርብላችሁ የቴሌግራም ቻናል ነው ቻናሉን በዚ ያገኙታል👉 @mhretab ለሌሎችም share ያድርጉ።
በቻናሉ ላይ ያላችሁን ማንኛውም አስተያየት ወይም ጥያቄ በዚህ bot ላይ 👉 @mhretabbot ወይም https://t.me/mhretabgroup group ላይ መጠየቅ ትችላላችሁ።

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-25 10:46:27
ነገ ሐምሌ 19 ቅዱስ ገብርኤል የሚነግስበት ምክኒያት ምንድን ነው
Anonymous Poll
68%
ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣን ከእሳት ያወጣበትን ቀን በማስብ
17%
ሰለስቱን ደቂቅ ከእሳት ያወጣበትን ቀን በማሰብ
11%
ድንግል ማርያም ወንድ ልጅ እንደምትወልድ ያበሰረበት ቀን
4%
መልስ የለም
587 voters3.4K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 21:57:10 ➢ ‹‹ #ባልንጀራህን_እንደራስህ_ውደድ።›› ዘሌ 19፡18፡፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

➢“አትበቀልም፥ በሕዝብህም ልጆች ቂም አትያዝ፥ ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ።”
ዘሌዋውያን 19፥18"

➢• ባልንጀራህን ውደድ የተባለው በሥላሴ አርአያ የተፈጠረውን ሰው በሰውነቱ መውደድ እንደሚገባ ለማመልከት ነው፡፡

‹➢‹ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃ አተኞችም በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።

➢የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ?

➢አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ።›› ማቴ 5፡42-48፡፡

➢• ጌታችን ትእዛዛትን ዘርዝሮ ባስረዳበት ክፍል ‹‹ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ፡፡›› ብሎአል፡፡ ማቴ 19፡19፡፡
➢• ባልንጀራን መውደድ ለሰው መልካም ሉቃ 10፡25-37፣ ነፍሱ የምትድንበትን ያዕ 2፡8-9 ማድረግን ያካትታል፡፡
•➢ ባልንጀራንም መውደድ ለራስ የሚሹትን መልካም ነገር ለባልንጀራ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ‹‹እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና።›› ማቴ 7፡12፡፡

➢• ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ነገረንም ባልንጀራን መውደድ ከራስ ጥቅምም የባልንጀራን ጥቅም መመልከትንም የተመለከተ ነው፡፡ ‹‹እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድስ እንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ፡፡›› ቀዳ ቆሮ 10፡24፣ ፊል 2፡2-4

➢• ባልንጀራውን የሚወድ ሰው ሰውነቱን በዝሙት፣ ሀብቱን በስርቆት፣ ስሙን በሐሰት በማጥፋት ወይም በሐሰት በመመስከር ባልንጀራው የሚጠፋበትን አያደርግም፡፡

➢• ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የትእዛዝ ፍጻሜ ግን ከንጹሕ ልብና ከበጎ ሕሊና ግብዝነትም ከሌለበት እምነት የሚወጣ ፍቅር ነው፡፡››ቀዳ ጢሞ 1፡5፡፡ እንዳለን፡፡

➢• ጌታችን ‹‹… ሁለተኛይቱም። ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትል እርስዋን የምትመስል ይህች ናት። ከእነዚህ የምትበልጥ ሌላ ትእዛዝ የለችም።… በፍጹም ልብ በፍጹም አእምሮም በፍጹም ነፍስም በፍጹም ኃይልም እርሱን መውደድ፥ ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት ሁሉ የሚበልጥ ነው አለው።›› ማር 12፡31-33፡፡


➢• እግዚአብሔርን መውደድና ባልንጀራን መውደድ አይነጣጠሉም፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን። ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ

ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።›› ቀዳ ዮሐ 5፡2-3፡፡
➢• ‹‹እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል።
ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ነፍሰ ገዳይም የሆነ ሁሉ የዘላለም ሕይወት በእርሱ እንዳይኖር ታውቃላችሁ። እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል። ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው፥ ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆን፥የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት ይኖራል? ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።››ቀዳ ዮ ሐ 3፡14-18፡፡

➢• ‹‹በብርሃን አለሁ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ። ወንድሙንም የሚወድ በብርሃን ይኖራል
ማሰናከያም የለበትም፤ ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥
ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና።›› ቀዳ ዮሐ 2፡9-11፡፡

➢ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን መውደድ የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ነው፡፡
➢‹‹ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን
እግዚአብሔርን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል? እግዚአብሔርንም እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።›› ቀዳ ዮሐ 4፡20-21፡፡

እንደተባልነው እንደራሳችን ባልንጀሮቻችንን እንድንወድ ይገባል፡፡
➢• ‹‹ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና፥ እርሱም፦ ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የሚል ነው።›› ገላ 5፡14፡፡
➢• ‹‹ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤ እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።›› ፊል 2፡3-4፡፡

➢• ‹‹አባትህንና እናትህን አክብር፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።›› ማቴ 19፡19፡፡
➢• ‹‹ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፦ ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።›› ማቴ 22፡39፡፡
➢• ‹‹ሁላችሁም በባልንጀራችሁ ላይ ክፉን ነገር በልባችሁ አታስቡ ፡፡›› ዘካ 8፡17፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

@mhretab
@mhretab
984 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 15:45:09 ትናንት ገንዘብን የሚቀሙ “እንዴት የሰውን ልፋት ይወስዳሉም ተብለው በተወገዙበት ምድር ሕይወትን የሚቀሙ፡ የሰው ዘር ቅነሳ የሚያደርጉ ግፈኞች ሲንጎማለሉ ማየት ያሳዝናል። ንጹሐን ወገኖቻችን እግዚአብሔር በሰጣቸው ማንነት ብቻ ሲሞቱ ስናይ የዝቅታችንና የመውደቃችን ልክ ማጣት ጎልቶ ይታያል። በርግጥ የሞቱት ወገኖቻችን ሰማዕታት ናቸውና ቤተ ክርስቲያን ትዘክራቸዋለች። ሰማዕት ስለ እግዚአብሔር ብሎ የሚሞት ነው። እነዚህም ወገኖቻችን እግዚአብሔር በሰጣቸው ማንነት፣ ለምን እንዲህ ተፈጠራችሁ ተብለው የሞቱ ናቸውና ሰማዕታት እንላቸዋለን። ገዳዮችም ቀጥተኛ የእግዚአብሔር ተቃዋሚዎች ናቸው። በወለጋና በጋምቤላ የአገራችን ክፍል የደረሰውን አሰቃቂ የወገኖቻችን ግድያ ስሰማ እንደ ወትሮው ልቤ በታላቅ ኀዘን ተመትቷል። በመላው የሀገራችን ክፍልም ክረምቱ ዓመት ከዓመት፣
ጠሉም የንጹሐን እንባ ሁኖ፣ “ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ" ያለው የጌታችን ቃል ደርሶ እያየን ነው። ጆሮ ከአቅሙ በላይ በሚሰማበት በዚህ ዘመን ያላችሁ ልጆቻችን አሁንም ልባችሁን እንደ ነቢዩ ዳዊት በእግዚአብሔር አበርቱ። ጠብና ክርክሩ እግዚኣብሔር ከፈጠረው ሰውነት ጋር ነውና እግዚአብሔር ፍርድ እንደሚሰጥ እናምናለን። የሃይማኖት አባቶችም የምናስተምረው ሕዝብ አልቆ ማንን ልናስተምር መሆኑን ደግመን ማሰብ ያስፈልገናል። አገራችን ኢትዮጵያ የሚያስከብሯትን መሪዎች አሁንም እየተጣራች ነውና መንግሥትና ሕዝብ ግፍን በተግባር ማውገዝ ያስፈልጋቸዋል። ነቢዩ ኤርምያስ በኀዘን ልቅሶው - የመቅደሱ ድንጋዮች በጐዳና ሁሉ ራስ ተበተኑ። ብሏል ሰቆቃ ኤር 4፡1። የሰው ልጅ ሕያው የእግዚአብሔር መቅደስ ነውና በየስፍራው ሲገደልና ቀባሪ ሲያጣ ስናይ ከነቢዩ ጋር ለማልቀስvእንገደዳለን። ጊዜው እየረፈደ፣ ሞትም ዜና እየሆነ፣ ዜጋም ክብሩን እያጣ ስጋትም ገዥ እየሆነ የምንቀጥልበት ጊዜ እንዲያበቃም ታላቅ ጥሪያችንን በሕያው እግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን! ሰኔ 16 ቀን 2014 ዓ.ም.

@mhretab
1.7K views12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 15:42:26
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት; በወለጋና በጋምቤላ የአገራችን ክፍል የደረሰውን አሰቃቂ የወገኖቻችን ግድያ አስመልክቶ ያስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት፤
*********
አዲስአበባ -ትዮጵያ
"""""""""""""""""""""
ሰኔ ፲፮ ቀን ፲ወ፬ዓ.ም
"""""""""""""""""""""
በስመ አብ ወወልድ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
"ወተዘርወ ዕንቊ ቅዱስ ውስተ ኩሉ ፍኖት
“የመቅደሱ ድንጋዮች በጐዳና ሁሉ ራስ ተበተኑ። ሰቆቃ.ኤር. 4፡1
አባታዊ የኀዘን መልእክት
የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በአገር ውስጥ እና በውጭ ያላችሁ የአገርን ክብር ለመጠበቅ በዳር ድንበር ያላችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤ ዘመናትን ፈጥሮ በሚገዛ፣ ዓለማትን በቃሉ በሚያስተዳድር፣ ለህላዌው መታጣት፣ ለጌትነቱ ዳርቻ
በሌለው በሕያው እግዚአብሔር ስም አባታዊ ሰላምታችንን እናስተላልፋለን።
ስሜትን በሚወርር፣ ልብን በሚያሳዝን፣ ጉልበትን በሚሰብር ኀዘን ውስጥ ላሉት ወገኖቻችን፤ ትናንት ባለ ብዙ ቤተሰብ ዛሬ ሌጣ ለሆኑት፣ የክብር ሞትና መቃብር ለተነፈጉት፣ ሰው ሆነው በሰው
ለተገፉት፣ ኢትዮጵያዊ ሁነው በኢትዮጵያውያን ለተሠዉት፣ አገር : ሳላቸው እንደ ባዕድ ለተቆጠሩት ለደከሙበት ምድር : በወርቅ ፈንታ ሰይፍ ለተከፈሉት ልጆቻችን እግዚአብሔር ያጽናችሁ በማለት፣ የሞቱትንም ደመ አቤልን ያከበረ አምላክ ደማቸውን እንዲመራመር በመለመን መልእክታችንን እንጀምራለን!
ብዙ መልካም ቃላት በሚነገሩበት፣ የጥበብ ድምፆች በሚያስተጋቡበት፣ መሠረት ፈርሶ ለጉልላት ጌጥ በምንጨነቅበት በዚህ ዘመን፣ “እንዴት ካለው ጊዜ ደረስን ማለት መመጻደቅ ባይሆን ኖሮ የሚባልበት ወቅት ሁኖ አግኝተነዋል።
1.5K views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 06:41:13
በኮተቤ ኪደነምሕረት የምትገኙ ባልማህተቦች በኪዳነምህረት
ዓውደምህረት ላይ ጌታ ለዮሐንስ የሸለማትን ድንግል ማርያምን በልደቴ ቀን ስለሸለማችሁኝ ክብር ያድልልኝ:: ለጉባኤው የሰጣችሁት ትኩረትና ያደረጋችሁት ዝግጅት ክህዝበ ክርስቲያኑ ወንጌል ወዳድነት ጋር ተዳምሮ ልዩ ነበር:: ሊቀመዘምራን ሀብታሙና የአካባቢው ወጣቶች አሁንም በርቱ::

@mhretab
1.3K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 12:24:45 ለሁላችሁም በጣም አመሰግናለሁ እግዚአብሔር ያክብርልኝ።
1.3K views09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 10:30:06
ሰኔ 16 ዕለተ ኪዳነምሕረት ይቺን ምድር ያየሁባት የልደት ቀኔ ናት። በዓላማ ወደዚች ዓለም ያመጣኝ እግዚአብሔር በዓላማ እያኖረኝ ነውና አመሰግነዋለሁ። ሀብት፣ ዝና፣ ሥልጣን ስላለን መኖር አንችልም። የመኖር ፈቃድ ሲሰጥ እንጂ፣ፈቃጁ ደግሞ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ክብር ለስሙ ይሁን።
1.6K views07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 13:49:24
ነገ ሰኔ 16 በኮተቤ ኪዳነምሕረት እንገናኝ የኪዳነምረት ወዳጆች ሼር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ::

@mhretab
1.5K viewsedited  10:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ