2022-08-23 20:56:10
#የሀዋሳ_ሕይወት_ብርሃን_ዓመታዊ_ኮንፈረንስ
ነሐሴ 16/12/2014 ዓ.ም
የ2014 ዓ.ም ዓመታዊው ኮንፈረንስ ሰኞ ነሐሴ 16/12/2014 ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት የጀመረ ሲሆን የመክፈቻ ንግግር፥ አገልጋዮችን የመቀበልና የመባረክ ጊዜ እንዲሁም ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ዘሌዋ.23:33-44 ያለው ክፍል በቤተክርስቲያኑቱ ዋና መጋቢ ፓስተር ጌቱ ተነቦ እና ተጸልዮ ተጀምሮ የጠዋቱ የአገልጋዮች ትምህርት ጊዜ ደግሞ በቄስ ትዕግሥቱ ሞገስ እና በዶ/ር ማሙሻ ፋንታ ቀጥሏል።
#ክፍል_አንድ/ አንደኛ ክፍለ ጊዜ
የእግዚአብሔር መጎብኘት
#በቄስ_ትዕግሥቱ_ሞገስ
ዘፍ. 50፥24
# ዮሴፍ ሕልምን እንጂ የሕልም ትርጉም አልገባውም ነበር
# ዮሴፍ ሕልሙን ቢያይም እግዚአብሔር ግን አስቀድሞ ከብዙ ዓመታት በፊት ለአብራሃም ነግሮታል።
# ዮሴፍ የልጁን ስም ምናሴ ብሎ ያወጣበት ምክንያት "የአባቴን ቤት አስረሳኝ" በሚል ትርጉም ቢሆንም ያዕቆብ ግን በዮሴፍ ሀሳብ የተስማማ አይመስልም። ምክንያቱም ዮሴፍ በግብጽ ምድር ምቾት ኖረ እንጂ የአባቱን ቤት የመርሳት ሁኔታ ላይ አልነበረም።
# የእግዚአብሔር የመጎብኘት ምስጢር ምንድነው?
* በሉቃስ ወንጌል ያለው ታሪክ የሁለት ወንድማማቾች ታሪክ፡ ታላቁ ልጅ ምን እንደተጠበቀለት አያውቅም ነበር። ሉቃ.15:11
* ዲና: የአባቷን ትልቅ ነገር ማየት ተስኗት ወደ ሌላ ሥፍራ ዓይኗን አቀናች (ወደ ሴኬም) ለጊዜያዊ ነገር እና ሰው ራሷን አሳልፋ ሰጠች። ዘፍ. 34:1-6
* ግያዝ በኤልሳዕ ላይ ያለው ትልቅ ነገር አልገባውም። ለዚህም ማሳያው የግያዝ ዓይኖች ኤልሳዕ ላይ ከነበረው ታላቅ የእግዚአብሔር እጅ ይልቅ ገንዘብ ላይ ያተኮረ ነበር።
* ዔሳው በምስር ወጥ ትልቁን የተጎበኘበትን ብኩርና ሸጠ።
# በኋላ ግን የእግዚአብሔር ጉብኝት የገባው ይመስላል።
# የዮሐንስ ራዕይ 20:11-
አንድ ቀን ሁሉም ሰው በፈጠረው አምላኩ (በእግዚአብሔር) ፊት ይቆማል። ማንም ሰው የሰራው ኃጢአት ሳይታይ አይበየንበትም።
በፍርድ ቀን ወደ ነጩ ዙፋን ፊት ስንቀርብ (በችሎት ጊዜ) ከምንጠየቅበት ነገሮች፦
1. የህሊና ክስ መዝገብ
#ህሊና ሲወቅሰን አልፈን ሄደን በምናደርጋቸው ነገሮች። ሰዎች የህሊናን ክስ ላለመቀበል ሲሉ ራሳቸውን (ህሊናቸውን) በተለያዩ አደንዛዥ ነገሮች ያስታሉ። ነገር ግን ከቆይየሰታ በኋላ ያ ያደነዘዛቸው ነገር ሲለቃቸው አሁንም ህሊና ክሱን ይቀጥላል። ከዚህ አልፈው ሄደው የሚፈልጉትን ነገር ሲያደርጉ ለሚፈልጉት ነገር ተላልፈው ይሰጣሉ። ህሊና በፍርድ ቀን እንደ black box ናት። ምክንያቱም በነጩ ዙፋን ፊት "ይሄን ያንን ተው ብለው እምቢ ብሎ አድርጓል" ብላ ትናዘዛለች።
2. የከንቱ ቃል የክስ መዝገብ
# ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው። ይህ ማለት እኛ በስሜት የምናደርጋቸው ክፉ ንግግሮች እና ስድቦች በነጩ ዙፋን ፊት ከምንጠየቅባቸው ነገሮች ዋንኞቹ ናቸው።
3. የተሰወረ የክስ መዝገብ
# እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ እንደሚያይ ያወቅን ግን ከሰው የተሰወረ የመሰለን። ሰዎችን ባስለቀስንበት ስውር ኃጢአታችን ይገለጣል።
4. የተገለጠ ሥራ የክስ መዝገብ
# በአደባባይ፥ በድፍረት፥ በጠራራ ጸሐይ፥ በትዕቢት እና በግፍ የተደረገ ክፋት ይገለጣል።
ይኼን ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ አስወገደው። ቆላ.2:14።
የእኛን ነገር እስከ አሁን የተጻፈብንን በክርስቶስ ኢየሱስ አስወገደልን። ከዕዳ ነጻ አደረገን። ወደ ነጩ ዙፋን ፊት መቅረብ የነበረብንን ነገር ግን ጌታ አስመለጠን። ስሙ ይባረክ
@menayae
@menayaediscussion
122 viewsNeba yedeva, 17:56