Get Mystery Box with random crypto!

Abdurahman Seid (ሜጢ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mettiey — Abdurahman Seid (ሜጢ) A
የቴሌግራም ቻናል አርማ mettiey — Abdurahman Seid (ሜጢ)
የሰርጥ አድራሻ: @mettiey
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.22K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-27 05:36:50 ረመዷን ⁵

እኔን ጨምሮ
- ምድራዊና ቁሳዊ ጉጉታችን እጅግ ስለበዛ፣
- አኺራ አለብን ብለን የምናስበው ሳንቀር እዚሁ ፍላጎት ስር ችንክር ብለን ስንቀርና፣
- አኺራን ባንክድም ለዱንያ የምንሰጠውን ያህል ትኩረት ስንነፈገው ጊዜ ነው ከሰሞኑ በዚህ ረመዷን ተጨንቄ የማስጨንቃችሁ።

እስቲ እነዚህን የሱረቱል ሙእሚኑን ተከታታይ አናቅፅ  እንመልከትማ። ስለ ሰው ልጅ የአፈጣጠር እርከኖች ይናገራል። አብረን ሕይወትን እንፈልጋለን እሺ

وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن سُلَالَةٍ مِّن طِينٍ

12) በእርግጥም ሰውን ከነጠረ ጭቃ ፈጠርነው፡፡

ثُمَّ جَعَلْنَاهُ نُطْفَةً فِي قَرَارٍ مَّكِينٍ

13) ከዚያም በተጠበቀ መርጊያ ውስጥ የፍትወት ጠብታ አደረግነው፡፡

ثُمَّ خَلَقْنَا النُّطْفَةَ عَلَقَةً فَخَلَقْنَا الْعَلَقَةَ مُضْغَةً فَخَلَقْنَا الْمُضْغَةَ عِظَامًا فَكَسَوْنَا الْعِظَامَ لَحْمًا ثُمَّ أَنشَأْنَاهُ خَلْقًا آخَرَ ۚ فَتَبَارَكَ اللَّهُ أَحْسَنُ الْخَالِقِينَ

14) ከዚያም ጠብታዋን (በአርባ ቀን) የረጋ ደም አድርገን ፈጠርን፡፡ የረጋውንም ደም ቁራጭ ሥጋ አድርገን ፈጠርን፡፡ ቁራጯንም ሥጋ አጥንቶች አድርገን ፈጠርን፡፡ አጥንቶቹንም ሥጋን አለበስናቸው፡፡ ከዚያም (ነፍስን በመዝራት) ሌላ ፍጥረትን አድርገን አስገኘነው፡፡ ከሰዓሊዎችም ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ፡፡

ثُمَّ إِنَّكُم بَعْدَ ذَٰلِكَ لَمَيِّتُونَ

15) ከዚያም እናንተ ከዚህ በኋላ በእርግጥ ሟቾች ናችሁ፡፡

አሰባችሁት ግን ? ታዲያ ሕይወት የት አለች? አስደንጋጭ አይደል? ይህን ሁሉ አስደናቂ አፈጣጠር ዘርዝሮ እየነገረን መጥቶ ምድር ላይ ትኖራላችሁ አላለም። ልክ የሆነች ቅፅበት አድርጎሳይጠቅስ አለፋትና ቀጥታ ወደ ሞት ሄደ። ሱብሐነል መሊክ! ለመጠቀስና መወሳት እንኳ ብቁ አይደለቺም። አላህ በቅዱስ ቃሉ ዘለላት።

ነብያችን (ሰዐወ) እንዲህ ይሉናል:-" ዱንያ ከአኺራ አንፃር አንዳችሁ አውራ ጣቱን ባህር ውስጥ አስገብቶ ይዛ የምትወጣውን ያህል መጠን እንጂ ሌላ አይደለችም።"

እስቲ ከዚህች ጣት ላይ ድርሻችንን እንፈልግ! ምን ያህል ናት? ለዚህች ዱንያ ነው አኺራ የሚሸጠው፣ ሰው እንዴት ጣቱ ላይ ባለች እርጥበት ከባህር ውሃ ይብቃቃል? ለርሷ ሲባል ወንጀል ይሰራል፣ ዝምድና ይቆረጣል፣ ታላቁን አምላክ እናስከፋለን። ዐቅል ያለው ሰው ይህን አያደርግም።

ኢስላም ሁሉን ትቶ ቁጭ ማለትን፣ ሌሎች ላይ ጥገኝነትንና ስራ አለመስራትን እጅግ ይጠላል። እንደውም ተከታዮቹ በራሳቸው የተብቃቁና ቁሳዊ ሕይወታቸው ሚዛናዊነትን የተላበሰ፣ ከምድርም ድርሻቸውን እንዳይረሱ አነሳሽ እምነት ነው። ድንበር አልፎ፣ ፍጡራንን ረጋጭና ፈጣሪን አስቆጭ እንዳይሆንም ይመክራል።

https://t.me/mettiey
447 views02:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 00:36:08 https://vm.tiktok.com/ZMYXyfjek/
454 views21:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 00:12:34

443 views21:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 14:40:14
https://t.me/kaayyoo_koof

Ramadan Nights
Lessons in Ramadan 2

Date : Sunday Ramadan 4 (March 26)

Time : 3:30 - 4:30pm local time

Live Stream on @kaayyoo_koof telegram channel

Join us and enjoy your best Ramadan Nights
504 views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 09:22:24 የመፅሐፍ ግብዣዬ ነው
66 views06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 05:30:10
ረመዷን ³

እርግጠኛ ሁን አንተ ስትሞት

- ዱንያ አታዝንም
-የዓለም እንቅስቃሴም ይቀጥላል
-ስራህን ሌሎች ይሰሩታል
-ንብረትህም ለወራሾች ይሆናል

አንተ ግን ሒሳብ ትደረግበታለህ

ስትሞት ቅድሚያ ካንተ የሚነሳው ስምህ ነው! ለዚያም ነው "አስክሬኑ የታል?" የሚሉት።
ሊሰግዱብህ ሲፈልጉም "ጀናዛውን አቅርቡት" ይላሉ። አፈር ውስጥ ሊያስገቡህ ሲፈልጉም "መይቱን ቀረብ አድርጉት" ይላሉ። ስምህ ትዝ አይላቸውም።

ለዚህ ሲባል ንብረት ዘርህ፣ ስልጣንና ልጆችህ እንዳይሸውዱህ። የምንሄድበት ዓለም ግዝፈትና ያለንባት ዓለም ከንቱነት ምን ያህል የተራራቀ ነው?

አሁን በሕይወት ያለኸው ሆይ! ስትሞት አንተ ላይ ሶስት ዓይነት ሃዘኖች አሉ
1) በደንብ የማይውቁህ ሰዎች ሐዘን:- ሚስኪን አላህ ይዘንለት ይሉሃል።
2) የጓደኞችህ ሐዘን:- ለሰዓታት ቢበዛ ለቀናት ያዝናሉ። ከዚያም ወደ ወጋቸውና ሳቅ ጨዋታቸው ይመለሳሉ።
3) ጥልቁ ሐዘን ቤት ውስጥ ነው። ሳምንታት፣ ወራት ከበዛ ዓመት ያዝናሉ። ከዚያም በትውስታ ማህደር ውስጥ ያኖሩሃል።

በሰዎች መሃል ያለህ ታሪክ አብቅቶ ትክክለኛው ታሪክህ ጀመረ። እርሱም አኺራ ነው። የሰራኸው ስራህ ሲቀር ውበትና ተክለቁመናህን፣ ንብረትና ጤንነትህን፣ ቤተሰብህንና መኖሪያዎችህን ተለየህ።

አሁን ጥያቄው ለቀብርና አኼራህ ምን አዘጋጅተሃል ነው?! ይህ ማሰብን የሚሻ እውነታ ነው። ግዴታ የተደረጉ ተግባራትን ብትፈፅም፣ ሱናዎችን ብታበዛ፣ ሚስጥራዊ ምፅዋትን ብትለግስ፣ መልካም ምግባርን ብትላበስ፣ የለሊት ሰላት ልማድህ ቢሆን ትድን ይሆናል።

ሟች ወደ ዱንያ መመለስን የሚመኘው ሰደቃን ለመስጠት ነው። ዑለሞቹ እንደሚሉት የምንዳውን ፋና ሲያየው ምነው ባበዛሁት ይላል። የቻልከውን ያህል መፅውት።

(ቅድሚያ ለራሴ ቀጥሎ ወንድም እህቶቼን ላስታውስ ተረጎምኩት)
501 views02:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 10:49:50
እጅግ በጣም አስቸኳይ

ይህ ወንድማችን አንዋር መሀመድ ይባላል። የድሬዳዋ ልጅ ነው። ይህንን ልጅ ወይም ቤተሰቡን የምታውቁ በዚህ ስልክ ይደውሉ።

09 30 30 80 81

09 44 72 69 85
242 views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 20:29:27
የሁሉም አቅጣጫዎች ስብራቶቻችን የሚጠገኑበት፣ ህመም ችግሮቻችን መፍትሔ የሚያገኙበት፣ ወደ አላህ እና ቀጣዩ ዓለም ቅርበትን የምንጎናፀፍበት ወር ያድርግልን።

አላህ ሆይ ! ረመዷንን የኢማን የአማን፣ የኢስላም የሰላም፣ የበረካና ኸይር ወር አድርግልን።
424 views17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 20:49:16 በረመዳን ምን ይጠበቅብናል?
==================
ቀልብ ህያው ሲሆን፣ የኢማን ጮራ በውስጡ ሲንቦገቦግ ሁለመና ወደ ቀኝ ይዞራል። ለመልካም ሥራ ይነቃነቃል። በየአቅጣጫው ለበጎነት ይነሳሳል። ጊዜ ሳይገድበው፣ በንቃት እና በተነሳሽነት ያለ አስገዳጅ ለኸይር ይዞራል።…
ቀልብን ህያው የሚያደርግ፣ ኢማን የሚያሳድግ፣ ሩሕን የሚያነቃ አዋጭ መንገድ ደግሞ የቁርኣን መንገድ ነው!

إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ

«ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በ͟ነ͟ሱ͟ም͟ ላ͟ይ͟ አ͟ን͟ቀ͟ጾ͟ቻ͟ች͟ን͟ በ͟ተ͟ነ͟በ͟ቡ͟ ጊ͟ዜ͟ እ͟ም͟ነ͟ት͟ን͟ የ͟ሚ͟ጨ͟ም͟ሩ͟ላ͟ቸ͟ው͟፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡»

እነሆ የቁርኣን ወር ከፊታችን ተደቅኗል!
ለቅዱሱ ወር ምን እናቅድ?!
ቀልባችንን ማረስረስ?! ህያው ማድረግ?! ውስጣችንን በኢማን መሙላት?! ረመዷንን ከረመዷን በኋላም በማይደበዝዝ ድምቀት ወሩን ሙሉ ማሳለፍ?
ወይስ ከዚህ ቀደም እንዳለፈው አይነት ረመዳን፣ ወሩ ሲያልፍ ደግሞ ታጥቦ ጭቃ የሆነ አዳፋ ህይወት መምራት!
ከረመዳን ምን እንፈልጋለን?!
:
የለጠፍኩላችሁ መፅሀፍ ከአመታት በፊት ይህንን ጥያቄ ለመመለስ የተከተበ ነው።
አንብቡልኝ! በዱዓም አስታውሱኝ!
377 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 21:17:36
ከቀናት ውስጥ ምርጥ የሚባሉት የረመዳን ቀናት ከፊታችን ተቃርበዋል። አልሃምዱሊላህ! እነዚህን ቀናት ያለብክነት እንድንጠቀምባቸው አቅዶ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ብልህነት ነው።

ረመዳን መድረሱን አስመልክቶ አስቤዛው፣ የቤት ፅዳቱ፣ ደስታው መዋከቡ፣ የምግብ ፕሮግራሙ እንዳለ ሆኖ ለነብሳችንስ በምን እንዘጋጅ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ለሁላችንም የቤት ስራ ነው።

የኑሰይባ ወግ ስብስብ እነዚህን የረመዳን ማድመቂያዎች እንዴት ማሰናሰል እንችላለን የሚለውን ለመወያየት፣ ልምድ ለመለዋወጥ፣ ከምሳሌዎቻችን ትምህርት ለመቅሰም የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 9 በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ቤተሰቦቻችንን ጋብዟል።

ብዙ ቅርንጫፎች እንዳሉት ቤተሰብ፣ የተለያየ የሕይወት ስንክሳር እንዳለባቸው ሴቶች፣ መግባባትን መርህ እንዳደረገ መሰናዶ ስለረመዳናችን እናወራለን። በረመዳን የቤት ውስጥ ስራን ቀለል ስለማድረግ፣ በብርቱ ነብሶቻችንን ስለማፅዳት፣ ወቅትን በአግባቡ ሳያባክኑ አንጥፍጥፎ ስለመጠቀም እናነሳለን፤ እንመካከራለን።

#የጀነት_ደጃፍ
#የኑሰይባ_ወግ
#ዋቢ_ሸበሌ_ሆቴል
#መጋቢት_9
#ቅዳሜ_7:30
#500 ብር

https://t.me/nuseybatalk
567 views18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ