2023-04-01 02:25:06
የዋሊያዎቹ ለአፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ተስፋ እና የአሠልጣኙ ዕጣ ፈንታ
---------------------------------------------------------------------------
አርብ መጋቢት 15/2015 በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ጊኒ ከኢትዮጵያ ምሽት 5 ሰዓት ሲጫወቱ ለማየት በርካታ ኢትዮጵያዊያን ቁጭ ብለው ጠበቁ።
ነገር ግን ውጤቱ ብዙዎችን ተስፋ ያስቆረጠ፤ አንገት ያስደፋ ነበር።
የዋሊያዎቹ የኋላ መስመር መፈረካከስ የተመቸው የጊኒ ካማኖ በ39ኛው ደቂቃ የመጀመሪያዋን ጎል አስቆጠረ።
ከእረፍት በኋላ አዲስ ነገር እናያለን ብሎ የጠበቀው ደጋፊ ተስፋ በ73ኛው ደቂቃ መነመነ፤ የጊኒው ባዮ ከሲላ የተሻገረችለትን ኳስ ከመረብ አገናኝቶ ጨዋታው 2 ለምንም እንዲጠናቀቅ ሆነ።
ሰኞ መጋቢት 18/2015 ምሽት 4 ሰዓት ኢትዮጵያ ከጊኒ የምድቡ አራተኛ ጨዋታ።
በዚህኛው ጨዋታ ዋሊያዎቹ ኳስን እንደልብ እያንሸራሸሩ መጫወት ቢጀምሩም ጊኒ በአምበሏ ናቢ ኬይታ አማካይነት በ4ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጠረች።
በጨዋታው ምርጥ ብቃት ካሳዩ ሦስት ተጫዎች መካከል አንዱ የነበረው ከነዓን ማርክነህ ከቸርነት ጉግሳ ያገኛትን ኳስ ከመረብ በማገናኘት ዋሊያዎቹ በአስደናቂ የቡድን ጎል አቻ እንዲሆኑ አስቻለ።
ከስምንት ደቂቃ በኋላ ጊኒዎች በሞሪባ ካሩማ አማካይነት ሁለተኛ ጎል በመድገም የኢትዮጵያን የማለፍ ተስፋ አመነመኑ።
ጨዋታው በጊኒ 3-2 አሸናፊነት ተጠናቀቀ። ኢትዮጵያም ከምድብ የማለፍ ተስፋዋም ደቀቀ።
ለመሆኑ ዋሊያዎቹ ውጤት እንዲህ የራቃቸው ለምንድን ነው? ጫና የበረታባቸው አሠልጣኝስ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆናል?
ሙሉውን ለማንበብ፦
@merkatotube @merkatotube_bot
1.2K views23:25