#DebreMarkosUniversity
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት የፈጠራ ሥራዎች ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የግልጋሎት ሞዴል ሰርተፊኬት ተሰጥቶታል።
ከእንሰት የሚዘጋጅ ጠላ እና አረቄ እንዲሁም የአዘገጃጀት ዘዴዎቹ ባለስልጣኑ ለዩኒቨርሲቲው የእውቅና ሰርተፊኬት የሰጠባቸው ፈጠራዎች ናቸው።
ፈጠራዎቹ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ በሆኑት ባዎቀ ጥሩነህ መገኘታቸውን
ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
በዩኒቨርሲቲው ሥም የተመዘገቡትን ፈጠራዎች እውን ለማድረግ ተቋሙ ሙሉ የምርምር ወጪዎችን መሸፈኑ ተገልጿል።
ፈጠራው ሙሉ ለሙሉ መተግበር ሲጀምር በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል ያልተለመደውን የእንሰት ምርት እና ጥቅም በሰፊው እንደሚያሳድገው ተመላክቷል።
Share&forward
Join
@merejamnch
@merejamnch
cross promotion መስራት የምትፈልጉ
Contact with me
@Gashtiman25