በወለጋ በአማሮች ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ፍጅት አስመልክቶ ለሚመለከታቸው ሁሉ መረጃ ብናደርስም አንዳችም የተግባር እርምጃ ባለመወሰዱ፤ በተለይም የአገር መከላከያ ሰራዊትን ጨምሮ የሚመለከታቸው የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት እና የፖለቲካ አመራሮች በቸልታ በማየታቸው ጭምር በሕዝባችን ላይ እስከዛሬ ከተፈፀሙት ጭፍጨፋዎች ሁሉ አስከፊው ጭፍጨፋ እየተፈፀመበት ይገኛል። የፌዴራሉ መንግስት ኮማንድ ፖስት አዋቅሮ በሚመራው የወለጋ አካባቢ በአማሮች ላይ እየተፈፀመ ያለው ፍጅት እንዲቆም መላው ሕዝባችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራትና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አስፈላጊውን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ ጥሪ አቀርባለሁ። 2.6K views13:20