2022-07-01 15:35:50
ደራሲ ከበደ ሚካኤል [ የቀጠለ ]
ደራሲ ከበደ ሚካኤል በአምስት አመታቱ የጣሊያን የአገዛዝ ዘመን ግን ከበደ ልዑል መኮንንን ለማስተማር ከመጡት መምህራን አንደኛው ሚስተር ሊሞይን የተባለ አቋቁመውት በነበረው ቤተ መፃህፍት ውስጥ እየተቀመጡ ብዙ የማንበብ ዕድል ስላጋጠማቸው ያ ዘመን በተደጋጋሚ አነበቧችው ተበለው ከተጠቀሱት መፅሃፍት አንደኛው ናፖሊዮን የተባለው መፅሃፍ ነው፡፡
ከንባቡ ጐን ለጐንም የጣለያንኛ ቋንቋን በሚገባ ተማሩ፡፡ ቋንቋን በተመለከተ ከበደ ሚካኤል ልሣነ ብዙ፡ ከሚባሉ ደራሲዎች አንዱ ናቸው፡፡ ከአገራቸው አማርኛና ግዕዝ ቋንቋዎችን ከውጭ ደግሞ ፈረንሣይኛን፣ ጣሊያንኛንና አንግሊዘኛ ቋንቋዎችን ጠንቅቀው ያውቁ እንደነበር የተረጋገጠ ነው፡፡
በሁሉም ቋንቋዎች የሚያገኙትን መፅሃፍት ታዲያ ለማንበብ አይቦዝኑም፡፡ ለከበደ ሚካኤል እንደ እጅ ማሟሻና እንደመጀመሪያ የሚቆጠረው ድርሰታቸው ብርሃነ ህሊና የተባለው ሲሆን የተጻፈው በጣሊያን ዘመን ነው፡፡ በኋላ የቅኔ ውበት በተባለው መፅሐፋቸው ከተካተቱት ስብስቦች አንደኛው በመሆን በተደጋጋሚ ታትሟል፡፡ ከበደ ሚካኤል ጠላት ከተባረረም በኋላ የድርሰት ሙያን እላቋረጡም፡፡
ከ1933 እስከ 1966 ዓም፡ በጋዜጠኝነት፣ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ በኢንስፔክተርነትና በምክትል ጻይሬክተርነት፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተርጓሚነትና በፀሐፊነት፣ በብሂራዊ ቤተመፅሃፍት ወመዘክር በዳሬክተርነት፡ እንደገና በትምህርት ሚኒስቴር በዳሬክተርነት፣ በንጉሠ፡ነገሥቱ ካቢኒ ከምክትል ሚኒስትርነት ማዕረግ የዜና ማደራጃ ኃላፊ እና በኋላም ሚኒስትር ሆነው ባገለገሉባቸው እጋጣሚዎች ሁሉ የድርሰት ሙያን አላቋረጠም።
በነዚህ የሥራ ዘመናት በርከት ያሉ መጽሃፍትን አሳትመዋል። ብዙዎቹ መፅሃፍቶቻቸወ፡ አራት ጊዜና ከዚያም በላይ እየተደጋገሙ ለመታተም በቅተዋል፡፡ በድርሰት ሥራዎቻቸው ትርጉሞች እና ወጥ ድርሰቶች ተውኔቶችና ግጥሞች የተካተቱ ሲሆን አሁን ድረስ ተወዳጆች ናቸው፡፡
ከበደ ሚካኤል ለመጀመሪያ ጊዜ እንግሊዛዊውን የተውኔት ደራሲ ሼክስፒርን ለኢትዮጵያ ተደራሲ ያስተዋወቁ በመሆናቸው የተለየ ሥፍራ አላቸው፡፡
ከበደ ሚካኤል በተደጋጋሚ ከአሳተሟቸውና በአንባቢውም ዘንድ ተወዳጅ ከነበሩ ድርስቶቻቸው መካከል የሚከተሉት በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ፡፡
የዶ/ር ደራሲ ከበደ ሚካኤል ሥራዎች
1. የእውቀት ብልጭታ(ትምህርት)
2. የመዠመሪያ እርምጃ(ትምህርት)
3. ታሪክና ምሳሌ ፪ኛው(ትምህርት)
4. ታላላቅ ሰዎች(ትምህርት)
5. የዓለም ታሪክ ፩ኛ ክፍል(ትምህርት)
6. ብርሃነ ሕሊና(ግጥምና ቅኔ)
7. የቅኔ አዝመራ(ግጥምና ቅኔ)
8. የቅኔ ውበት(ግጥምና ቅኔ)
9. ጃፓን እንዴት ሰለጠነች(ትምህርት)
10. የትንቢት ቀጠሮ(ተውኔት)
11. አኒባል(ተውኔት)
12. በላይነህ/ የቅጣት ማዕበል(ተውኔት)
13. ካሌብ(ተውኔት)
14. አክዐብ(ተውኔት)
15. ቅዱስ ገብርኤል በምድረ ገነት(ተውኔት)
16.ትልቁ እስክንድር
17. ከይቅርታ በላይ
18. የሥልጣኔ አየር
19. የልዑል መኮንን ታሪክና መታሰቢያ በሥዕል
20. የድርሰት ትንሣኤ
21. ግርማዊነታቸው በአሜሪካን አገር
22. ኢትዮጵያና ምዕራባዊ ሥልጣኔ
23. ሥልጣኔ ማለት ምንድነች? ይገኙባቸዋል፡፡
ከላይ ከተጠቀሱት አንዳንዶቹ በስብስብ መልከ በድጋሚ የተጻፉ አሉ፡፡ ለምሣሌ የቅኔ ውበት የሚለው መፅሃፍ የስብስቦች መጠሪያ እንጂ በራሱ የተለየ ድርሰት አይደለም።
ከበደ ለዚህ ሁሉ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን እግኝተዋል፡፡ በ1957 ዓ ም በአማርኛ ስነ ፅሁፍ የመጀመሪያው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሽልማት ድርጅት ተሽላሚ ለመሆን በቅተዋል፡፡ በ1990 ዓ.ል ደግሞ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ከአዲስ አበባ ዩኒሽርስቲ ተቀብለዋል፡፡
በ1991 ዓ.ል በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ:
ከበደ ሚካኤል ከ1966 ዓ.ል ለውጥ በኋላ ብዙ ችግሮች ደርሰዉባቸዋል። የሰሩት ቤት በመወረሱ አብዛኛዉን ኑሯቸውን የገፉት አውራሪስ እና ቱሪስት በተባሉ ሆቴሎች ውስጥ ነዉ: “አምሮቸዉ ንክ ሆኗል” እያሉ በሚያስወሩባቸው ወገኖች አማካኝነትም የመገለል ችግር አጋጥሟቸው እንደ ነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የወታደራዊ ደርግ ባለስልጣናት በደራሲነት ለአገራቸው ያበረከቱትን የስነ ጽሁፍ ስራ ከመመልከት ይልቅ የወደቀዉን ስርዐት ግብረበላ ነበሩ ከሚል ድምዳሜ ላይ በመድረሳቸው ቤታቸዉን በቀበሌ ታጣቂዎች ካለአግባብ መነጠቃቸውን እና በችግር ላይ መሆናቸውን እያወቁ አንዳችም መፍትሄ ሳይሰጧቸው አንደቀሩ በቁጭት የሚያስረዱ ወገኖች አሉ። አንዳንድ የደራሲ ከበደ ሚካኤል መጽሃፎች አሁንም ታትመው በገበያ ላይ ይገኛሉ ።
ተፈፀመ @maraki_layrics
101 views12:35