Get Mystery Box with random crypto!

ማራኪ ስነ-ፅሁፍ

የቴሌግራም ቻናል አርማ maraki_lyrics — ማራኪ ስነ-ፅሁፍ
የቴሌግራም ቻናል አርማ maraki_lyrics — ማራኪ ስነ-ፅሁፍ
የሰርጥ አድራሻ: @maraki_lyrics
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 682
የሰርጥ መግለጫ

በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ!!! ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ፡ በቻናላችን ማራኪ ፣ አዝናኝና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ ስነ -ፅሁፎችን ፡ ከተለያዩ የስነ-ፅሁፍ ባለሙያዎች ወደ እናንተ ይዘን እንቀርባለን።
https://t.me/ n3xAcsHqjJNlNDg0
ሀሳብና አስተያየት በ @Muke_ye ያድርሱን

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-28 19:04:20 ያልወደደ አበደ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
በሰው የደረሰ...
በኔ ላይ እንዳይደርስ ፣ ስፈራና ስቸር
ወድጄሽ እንዳላብድ ፣ ስጠነቀቅ ነበር፡፡
ታድያ ምን ያደርጋል
በከንቱ ፍርሃት ፣ ባክኖ መጠንቀቄ
ዋናው እብደት ነበር ፣ ከመውደድ መራቄ፡፡

@maraki_layrics
104 views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 13:47:50 ​​ላ’ንዲት የገጠር ሴት

ስትፈጭ የኖረች ሴት፣
መጁ በመጠኗ፣ ወፍጮውም በልኳ፣
ጓያ ትፈጫለች
ጓያ ሽሮ ሲሆን ያበቃል ታሪኳ !!

አስባው አታውቅም…
ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደመጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ከና’ቷ ሆድ ወጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ለባሏ ተሰጠች……

ተዚያን ቀን ጀምራ፣
ተዚያን ቀን ጀምሮ፣
ድንግል ድንጋይ ወቅራ፣
ትፈጫለች ሽሮ……

አታውቅም፣
ማን እንደሚባሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣
አታውቅም፣
ሹማምንት በ’ሷ ስም፣ ምን እንደሚሠሩ፣
አነሳኹት ‘ንጂ፣ እኔም ለነገሩ፣
ፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ፣
ምን ይጠቅማትና ጓያዋን ለማድቀቅ

ከቶ ማንም የለ, አበባ ‘ሚሰጣት፣
ከቶ ማንም የለ፣ ከተማ ‘ሚያወጣት፣
ከቶ ማንም የለ ፣ በዳንኪራ መላ፣ ወገቧን የሚያቅፋት፣
ልፋቷም፣ ዕረፍቷም፣
ወደዚህ መጅ መሳብ
ወደዚያ መጅ መግፋት……
እንደ ዓባይ ፏፏቴ፣
ሽህ ዓመት ቢንጣለል፣
ቢጎርፍም ዱቄቱ፣
እንደ ሲኦል ወለል፣ ጫፍ የለውም ቋቱ!

ከዘመናት ባንዱ
መስተዋት ፊት ቆማ፣ በተወለወለው፣
ራሷን ለማየት፣
ከጸጉራ ላይ ያለው
ዱቄት ይኹን ሽበት ሲያቅታት መለየት፣
ያኔ ይገባታል
የተሰጣት ዕጣ፣
ከማድቀቅ ቀጥሎ፣ መድቀቅ እንዲመጣ…

የመጅ አጋፋፏ - አምሳለ ሲሲፈስ፣
ከቋት ሥስት እንጅ፣ ሢሳይ አይታፈስ፣
ትቢያ ‘ሚተነብይ ዱቄት በዙሪያዋ፣
ከባርኔጣ አይሰፋም፣ የኑሮ ጣሪያዋ፣
"ስትፈጭ የኖረች ሴት"
ይህ ነው መጠሪያዋ!
በእውቀቱ ስዩም

@maraki_layrics
117 viewsedited  10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 10:44:41 ወቀሳ & ምክር

ጊዜውን ባነጻጸረ ሁነትና ቋንቋ
የተጻፈ!
በሰኢድ አህመድ

መች ትርጉም ሊኖረው
ሃይ ሃይ መባባሉ፣ እኔ አንችን ወደድኩ
ቻት ላይ ተቸካክሎ ሃይ ሃይ መላላኩ፣
መሽኮርመም ማፈሩ ከንቱ መግደርደሩ
ላንቶፋንቶ ወሬ
ስልክ ላይ አፍጥጠው ሳይተኙ ማደሩ

መች ትርጉም ሊኖረው ከመጃጃል በቀር
መገናኘት መዞር በስሜት መፋቀር
መቃጠር መሽቀርቀር መኳል መቀባባት
ከዚያም ከትንሹ አልፎም ከትልቁ
ወንጀል ውስጥ መግባት
ሃይ ሃይ መባባሉ
ታዲያ መች ሆነና የኸይር መነሻ
ከአሏህ አርቆ ወንጀል አስመርቆ
ባይ ባይ ካስከተለ በስተመጨረሻ

ሞትኩልሽ ዳንኩልሽ ተንፈራፈርኩልሽ
በሚል የይምሰል ቃል አንጀቷን ከመብላት
ጓጉለህ ከማጉላላት
ካፌ እያነፈነፍክ ሻይ ከማስፈላት
አልበም ፎቶ እየላክ ስልኳንም ከመሙላት

የእውነት ከወደድካት
ወንጀል ሳትነካ ሃራም ሳታስነካት
በሃላሉ መንገድ አግባና ውሰዳት

እንጂማ በከንቱ መንገለጃጀጁ
በየ ጉራንገሩ እየተሸጎሩ ማሳጁ ሜሴጁ
ላይበጅህ ላይበጃት ሊጎዳህ ሊጎዳት
አታፍስስ አትቅዳት
የውነት ከወደድካት፣ አግባና ውሰዳት

ሌላ እንዳያገባት ልቧን አሸፍተህ
ሌላ እንዳታገባ ቃልህን ሰጥተህ
ወይ አንተ አታገባት ወይ አትለቃት ፈተህ
በስሜት መጃጃል በወጥመድ አግተህ
ማይሆን እያሳሰብክ ከምታስጨንቃት
ተው አርገህ ልቀቃት፣በከንቱ አትሸውዳት
ወንድ ከሆንክ ደሞ ፣አግባና ውሰዳት

አንች ንግስቲቱ ፈላጭ ቆራጪቱ
በወንዱ አንደበት ምትቆላበሺው
ሃይል አለሽ ካወቅሺው
አዎን አቅም አለሽ ጀሊሉ ያደለሽ
ፈሪውን ሚያጀግን ዝንጉን የሚያነቃ
ሰነፉን ሚያጠና ሀዘን የሚያፅናና
ሃይለኛን ሚያጠቃ
የሹም ያገር መሪ የጦር ፊት አውራሪ
የወንዳ ወንድ ሁሉ አንችው ነሽ አለቃ

አንች ከሆንሽ በሳል ማትረክስ ማትጣል
ባንችው ስር ቢያድር እንጂ ወንድ ምን ያመጣል
አንችው ፊት ሰጥተሽ ፣ ብልህ መሆን ትተሽ
ነካክተው ሲተውሽ
ምን ትርጉም ሊኖረው ማልቀስ ቤትሽ ገብተሽ

አዎን ንግስት ነሽ የላይም የታች
ግን ካወቅሽበት ነው መሆንሽን አንች
የቁልፏ ባለቤት ዘጊና ከፋች

የእውነት ከወደድሽው ከልብ ከከጀልሽው
በፎቶ አታምሽው፣ አታመላልሽው
በሌሊት ደውለሽ አትረባብሽው
ሁሌም በቅፍሽ ስር ገብቶ እንድታይው
ሽማግሌ ልከህ ኒካህ እሰር በይው

እሽ ካለ መልካም
ይኸው ነው ቁም ነገር አይከስምም አይጃጅም
ግን ኒካህ ሲነሳ ምክኒያት ካሸከመሽ
ቦልኪው በቶሎ ለጅል አትታመሽ
አሁኑን በቶሎ ሳትውይ ሳታመሽ

ለስሜት ተማርኮ ወንጀል ከመቃረም
ሳይመሽብን ቶሎ ይሻላል መታረም

@maraki_layrics
97 views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 08:13:09 ድንጋይን ታቅፎ ዳቦ ነው ለሚል ሰው
ብላው ነበር ምሱ
ያኔ ልክ ይገባል ሲረጋግፍ ጥርሱ።
በግዱ ያምነኛል አይልም ዘንበል ቀለስ
በጥርሱ እንዳልመጣ በድዱ ሲመለስ
ግን አሁን ጉድ መጣ
የማለ ይመስል ከስህተት ላይወጣ
ብላው ስለው በልቶት
የታቀፈው ስህተት ጥርሱን አሳጥቶት
ስህተቴን ለመተው መች እላለሁ በጂ
ጥርስ የሚያረጋግፍ ዳቦ እላለሁ እንጂ
ነበረ ምላሹ
ምን ቢቀር በድዱ ከጥርሱ ኮብልሎ
ነገ ያስተክላል
ኪሱን ስላወዛው ዲንጋን ዳቦ ብሎ
ዳሩ ምን ሊረባ
ለየቅል ነው ፍቹ ምርትና ገለባ
ኪስህን እያየች ምላስህ ብትክድም
አንተንና ዳቦን መለያየቱ ግን
ለኔ አይነቱ አይከብድም።
።።።።።።።።።
ሰኢድ አህመድ

@maraki_layrics
86 viewsedited  05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 19:45:31 እንደ ክረምት ዝናብ
ችግሬ ይረግፋል
ምስኪን ትከሻዬ
እሱን ይቀበላል
ሰዎቹም ይላሉ
እንዴት ቻለው እሱ
ሁሌም ብልጭ ይላል
አይከደን ጥርሱ
የተበደለ ሰው
ችግር ላላት ነፍሱ
ኑሮ እንዴት ነው ቢሉት
ፈገግታ ነው መልሱ
ይስማዕከ

@maraki_layrics
110 viewsedited  16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 14:53:22 በአንድ ወቅት የተከሰተ እውነተኛ ገጠመኝ

የተከፈለ ውለታ

አሜሪካን ካንሳስ ሲቲ ነዋሪ የሆነችው ሳራ ዳርሊንግ ከስራ ወጥታ ወደ መኖሪያዋ በማቅናት ላይ ሳለች አንድ በዕድሜ ጠና ያሉ አዛውንት ከመንገድ ዳር ቁጭ ብሎ ሲለምን ትመለከታለች።

ሳራ ወደ አዛውንቱ በመጠጋት ቦርሳዋን ከፍታ የተወሰኑ ዶላሮችን በማውጣት ሰውየው ከጎኑ ባስቀመጠው የፕላስቲክ ኩባያ ውስጥ አኑራ ጉዞዋን ትቀጥላለች።

ሳራ ከምንግዜውም በላይ በህይወቷ ደስተኛ ነበረች ከምትወደውና ከምታፈቅረው ጓደኛዋ ጋር በትዳር ለመጣመር የቀናት ዕድሜ ቀርቷቸዋል።

ለእሷ ከፍተኛ ክብርና ፍቅር ያለው ፍቅረኛዋ እጅግ ውድ የሆነ ዳይመንድ የቃል ኪዳን ቀለበት ገዝቶ በጉልበቱ ተንበርክኮ የታገቢኛለሽ ጥያቄ ካቀረበላት እና በደስታ እሺ ካለችው ጊዜ አንስቶ ህይወቷ በሀሴት ተሞልቷል።

ምሽት ላይ እንደተለመደው በስስት የምታየውን የዳይመንድ ቀለበት ስማ ለመተኛት ቦርሳዋን ከፈተችው በድንጋጤ ደርቃ ቀረች ቀለበቱ በቦታው አልነበረም።

ቦርሳዋን የከፈተችው መንገድ ዳር ቁጭ ብሎ ለሚለምነው አዛውንት ገንዘብ ለመስጠት ብቻ እንደነበር አስታውሳ የሰውየው ገንዘብ መሰብሰቢያ ኩባያ ውስጥ ቀለበቱን አብራ ማኖሯን አስታወሰች።

ለእጮኛዋ ስልክ በመደወል ሁኔታውን አጫወተችው እጮኛዋም ሲከንፍ መጣ
ተያይዘው በልመና ወደ ሚተዳደረው ሽማግሌ ቦታ ሄዱ። ሰውየው በቦታው አልነበረም "በእርግጥ ውድ የሆነ ቀለበት አግኝቶ እንዴት ተመልሶ በቦታው ሊቀመጥ ይችላል" የእጮኛዋ ግምት ነበር።

በቀጣዩ ቀንም በተመሳሳይ ከእጮኛዋ ጋር ሽማግሌው ተቀምጦ ወደ ሚለምንበት ቦታ ሄዱ አሁንም ሰውየው አልነበረም። በቃ ጦስሽን ይውሰድ ከእንግዲህ እርምሽን አውጪ ነበር የእጮኛዋ መልስ። በሦስተኛው ቀንም ሳራ ለእጮኛዋ ደውላ ወደ ሽማግሌው ቦታ እንዲሄዱ ጠየቀችው እጮኛዋ በመገረም "6 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ቀለበት ችግረኛ እና በረንዳ የሚያድር ሰው እጅ ገብቶ አገኘዋለሁ ብለሽ እንዴት ታስቢያለሽ?" ነበር ያላት... ሳራም በቃ የዛሬን ብቻ እንየው ሰውየው ከሌለ እርሜን አወጣለሁ አለችው።

እጮኛዋም የሳራን ፍላጎት ለመሙላት ተስማምቶ ጉዞዋቸውን አቀኑ ሽማግሌው በቦታው ተቀምጦ ሲለምን አገኙት
ሳራ በደስታ ተዋጠች አላውቅሽም ብሎ እንዳይሸመጥጠኝ የሚል ስጋት እንደዋጣት ወደ ሽማግሌው ተጠጋች።

አባት ያስታውሱኛል? በማለት ጠየቀች። ሽማግሌው ቢል ሬይ ሀሪስ ይባላል ቀና ብሎ ተመልክቷት አላወቅኩሽም ልጄ ሲል መለሰላት።

ሳራም ከ3 ቀን በፊት ከቦርሳዬ ገንዘብ አውጥቼ ሳስቀምጥ ሌላ ዕቃ አብሬ አኑሬ ነበር?!
የጣት ቀለበት ነው?
አዎን አባት…
ቢል ቀለበቱን ጠቅልሎ ካስቀመጠበት ኪሱ በማውጣት አንድ ቀን እንደምትመለሺ አውቅ ነበር በማለት ከሰጣት ብኋላ... ቀለበቱን ያገኘሁት ዕለት ትክክለኛ ወይም አርቴፊሻል ቀለበት መሆኑን ለማወቅ ወደ ጌጣጌጥ ሱቅ ወስጄው ነበር እነሱም ትክክለኛ መሆኑን ነግረው $4,000 ዶላር ሊገዙኝ ጠይቀውኝ ነበር።

በእርግጥ ኑሮውን በበረንዳ ለሚያሳልፍና በልመና ለሚተዳደር 4ሺህ ዶላር ከፍተኛ ገንዘብ ነው። ነገር ግን እኔን ለመርዳት ብላ በስህተት ቀለበት የጣለችን ሴት ንብረት መንካት አልፈለግኩም። በመሆኑም በጥንቃቄ አኑሬው የአንቺን መምጣት ስጠባበቅ ነበር ሲል መለሰላት።

ሳራ ዳርሊንግ እና እጮኛዋ የመልካሙን ቢል ሬይ ሀሪስ ታሪክ ቀለበቷን ሲሰጣት ከሚታይ ምስል ጋር በማያያዝ ለሶሻል ሚዲያ (Facebook) አበቁት። ከታሪኩም ጎን ለጎን የእርዳታ ማሰባሰቢያ ጎፈንድሚ አካውንት ከፈቱ በቢል ሬይ ቀናነት እጅጉን የተደሰቱ አያሌ ግለሶቦች የዕርዳታ እጃቸውን ይዘረጉ ጀመር በአጭር ጊዜ ውስጥ 260,000$ ዶላር ተሰበሰበለት።

በአሁን ሰዓት ቢል ከበረንዳ አዳሪነት ወጥቶ የቤት ባለቤት ሆነ ተጨማሪ የመጦሪያ ገንዘብም አገኘ።

መልካምነት መልሶ ይከፍላል።

@maraki_layrics
97 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 21:30:42 …ምንም አልል…

እሺ እንዲህ በዝምታ
የልቤን ደም ስር ትርታ
የደቂቃ እድሜን ትዝታ
ትር ስትል አፍታ ላፍታ
እያዳመጥኩ እያስታመምኩ÷
ጊዜዬን እያሰላሰልኩ
ሳልናገር ሳልጋገር÷
እየደገምኩ እያሰላሰልኩ
ሳልሰለች እየመላለስኩ።
እሺ እንግዲህ በፀጥታ
የልቤን ደም ስር ትርታ
የእስትንሴን ቃል ጉምጉምታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
ሳልሰለች እየደጋገምኩ
በእግረ ህሊና እየደቀኩ
እየቓጠርኩ እየቆጠርኩ
እሺ እንግዲህ አልናገርም
ባ'ንደበቴ አልተነፍስም
በልሳኔ አልመሰክርም
አልልም፤ ምንም አልልም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም።
የልቤን ደም ስር ሲያቃጭል
ልሳኔን ሲያስነሳ ሲያስጥል
ቃላቴን ሲቃኝ ሲያጋግል
ትንፋሼን ሲያንር ሲያዳውል
ክል ሲል ትር ድው ሲል
ማዳመጥ ማስታመም እንጂ÷
ሌላ ምንምምም አልል።

ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን

@maraki_layrics
106 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 21:23:10 ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!""

ሰዎች በእኔ ላይ ምን እንደሚያስቡ ለማወቅ የታገልኩትን ያህል ራሴን ለማወቅ ብሰራ ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

በፍጹም የማይፈልጉኝን ሰዎች ስለማመጥና ስከታተል ያሳለፍኩትን ጊዜ ለእኔ ዋጋ ላላቸው ሰዎች ሰጥቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

በማያገባኝ የሰዎች ስራና ሃሳብ ላይ በማውራትና በመቃወም ያባከንኩትን ጊዜ የሚደገፍ ሰው ፍልጌ ደግፌ በሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

በየጊዜው ካለእቅድ የማወጣቸውን የገንዘብ መጠኖች በጥንቃቄ ብቆጥባቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ምንም ያህል ብጨነቅ መለወጥ በማልችላቸው ነገሮች ላይ መጨነቄን ትቼ ለመለወጥ አቅም ያለኝ ነገሮች ላይ አተኩሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

የሚወዱኝ ቤተሰቦቼና ጓደኞቼ ሲመክሩኝ የመስማትና ጥሩውን ምክር የመቀበል ልማድ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ለመጀመር ያሰብኳቸውን እነዛን ወሳኝ ነገሮች ጀምሬያቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

የማይሆኑ የማሕበራዊ ሳይቶችን ሳስስ ያመሸሁባቸውን ምሽቶች የቀኑን ውሎየን ለመገምገምና ለነገ በማቀድ ባሳልፋቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ለየእለት ገጠመኞች ምላሽ እየሰጡ ከመሯሯጥ ይልቅ በራእይና በዓላማ ኖሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ያም ሆነ ይህ ያለፈው አልፏል! አሁንም ቢሆን አልመሸም!
እሩጫህን ቀጥል

@maraki_layrics
191 views18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 09:03:27 "...የሰፋ ሀገር ይዘን፣ ጠቦ መሞት ይብቃን፤..."

(ገጣሚት፥ ህሊና ደሳለኝ)
---------------------
አይችለው የለ እንጂ - የልባም ትከሻ፣
ከውርደቱ ደጃፍ - ነውሩን ማምለጥ ሲሻ፣
ገርፎ ማሳመን ነው፣ የፈሪ ሰው በትር፣ የሽንታም ሰው ጋሻ።

እንመን ግድ የለም…

ፍትሕ አይታለምም - ሐቁን እየሸሹ፣
የጠፋው እንዲገኝ፣ እስኪ መጀመርያ፣ ይፈተሽ ፈታሹ፤

አቀርቅራ ታዝግም፣ ትጎናበስ እንጂ፣ መሔድ እስኪያድላት፣
ሰብረህ ስታበቃ፣ 'ምርኩዝ እንቺ' ብለህ ደርሰህ አትደልላት፤

'በኔ ብቻ' በሽታ - ጥበት እየቀጣን፣
በ'ናታችን ርስት፣ ባባታችን መሬት፣ መደገፊያ እያጣን፤

ቁልቁል እያሰቡ - ምንድነው ከፍታ፣
መብት እየነጠቁ - ምንድነው ግዴታ?
እስከ መቼ ተረት - ግዴለም ይነጋል፣
መንገድ እየቀሙ - ምርኩዝ ምን ያደርጋል?

አንተ እንደሁ ልማድህ አለስልሶ መግደል አሳስቆ መግፋት፣
'ካብኩ' እያሉ 'ማቅለል' 'ሳምኩ' እያሉ 'መትፋት'፣
የበደል ላይ ጀግና - ሬሳ ላይ መዛት፣
መዋረድን ሽሽት - የአሽቃባጭ አፍ መግዛት፤

እየሸሹ ትግል - እየሮጡ ዛቻ፣
በጉንዳን ልቡና - የነብር ዘመቻ፤

የበላ እያሠረ - የቀማ ቢገፈው፣
የሳተ እያረመ - ያጠፋ ቢገርፈው፤

ጀግና ልማዱ ነው፣ ባርያ ሆኖ ታሽቶ፣ ንጉሥ ኾኖ መግዛት፣
እያነሰ ገዝፎ - እየሞተ መብዛት፤

ያ ሽንታም ላመሉ - በሬሳ ይፎክራል፣
ከፈሪ ገዳይ 'ድል' - የጀግና 'ሞት' ያምራል፤

ይልቅ……

በእኔ ልቅደም ትርክት- የዘር ደዌ አያጥቃን፣
ከጎጥ ቀንበር ፍቱን - ጠቦ መሞት በቃን፤

የጸደይ ወይን ኾኖ - የሐቅ እንባ ቢጥም፣
በድሎ መጀገን - ጀብድ ሆኖ ቢረግጥም፣
የትግላችን ልኩ - ያሳር ደም ቢያስምጥም፣
በሰፋ ሀገር ጠበን - ኢትዮጵያን አንሰጥም!!!

ህሊና ደሳለኝ
136 views06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 15:57:40 መጅኑኑ ለይላ
(ሰኢድ አህመድ)

ከህል ውሃ አጣልቶ፣
ከፌሽታ ከሳቅ ጫወታ
ከጤና ዐውድ አመንኖ ፣
ከረፍት ከንቅልፍ ከመኝታ
ለብቻ አርጎ እያስወራ ፣
በብቻ ቀልድ እያሳቀ
የህላዌ ግብረ ገብን
እየፋቀ እያራቀ
የባይተዋርነት ግብሩን
ያላምዳል ያስወድዳል
ባስ ሲል ሲጠና ደግሞ
በጤና ስም ያሳብዳል

በፍቅር መያዙ ይፋ እንዳይወጣበት
ስሜቱን ሊሸሽግ ቢለጉም አንደበት
ቋንቋም ቢጠፋበት
ማፍቀሩን ሊሰውር ከሰው ቢዘነቅም
ልቡ ተንሰቅስቆ በጥርሱ ቢስቅም
ቅሉ ትንግርት ነው ፍቅር አይደበቅም
አይንን አበልዞ እጅ እግርን አፍዝዞ
ውስጥ ውስጡን መዝምዞ
የራሱኑው ቋንቋ ባፍቃሪ ጠርዞ
ፍቅር ቡልቅ ይላል
ደምቆ ቦጎ ልቆ
አንደበት ያባውን ባከላቱ አዝልቆ
ቢመሽጉት ዋሻ ቢዶሉት ዱር ገደል
ሆኖ እንደመታደል
ፍቅር ለመታወቅ አያሻውም ፊደል

የለይላዋ መጅኑን
ቀይስ ተብሎ ነበር ፣ስሙ የጠደቀው
ያኔ ፍቅርን ሳያውቅ ፍቅርም ሳያውቀው
ሳቂና ተጫዋች ሃር ነው ፀዐዳው
ያኔ ውብ እያለ ልቦናው ሳይከዳው
መደዴ ነበረ ስጋውን ከፍትፍት
ያኔ ጤና ሳለ ስስ ልቡ ሳይሸፍት
ወሸኔ እረኛም ነው አውሬ ሁሉ ሚያፍረው
ፍቅር የሚሉት ጉድ ገብቶ ሳያነፍረው

ዛጎላማ አይኖች፣ ብርንዷማ ጉንጮች
በርታ ምታበራ ከጨረቃ ሙዳ
ገና ከልጅነት አብራው መስክ ወርዳ
ከረኝነቱ ጋር በግ ፍየል አግዳ
በሱ አይን ያፈሰች ተወህቦ ናዳ
ከከናፍሮቿ ማር የምታስቀዳ
ይኸ ይቀራታል ማትባል ኮረዳ
የሷ አደረገችው ልቡን ይዛ ሄዳ
ለይላን ሲል አንግቶት ለይላን ሲል መዋሉ
ተጣፋበትና የረኝነት ውሉ
ተጣልቶት አረፈው ከበግ ከፍየሉ

ያሰላስላታል፣
ባጥንቱ ላይ ቡርሽ ፣ በደሙም ላይ ቀለም
በልቡ ላይ ሸራ ፣ ይጠበብባታል
ይፅፍ ይስላታል።
ማሰብ ማሰላሰል፣
የሰባ ገላውን አመንምኖ አከሳው
ከለይላ በቀር ስሙን ሁላ እረሳው
የርሱን የበግ ቅፍለት ቢከበው ተኩላ
ግልገል ፍየል ብትሮጥ መንጋዎቿን ጥላ
መች ግድ ሊሰጠው፣
የለይላ ፍቅር በልቡ ላይ ፈጎ
ያሳየዋልና
ፍየሉን ተኩላ ጅቡንም በግ አርጎ

ቅኔው ፣ ዜማው ግጥሙ
በስሟ ጓጉጦ መዞሪያ ቅኝቱ
ለይላየ፣ ላይላዋ ፣ ለይላይቱ ለይላ
ሲል ያቆላብሳታል፣ የርሱ አንደበት ገላ
አይናገር ነገር፣ ይፋ አያወጣው
የሸበበው ፍቅሯ ድፍረቱን አሳጣው
አልቀረበት ነበር በርሷ መወደዱ
ዝም አስብሏት እንጂ
የሴትነት ወጉ፣ ህጉ ዘ ልማዱ
የፍቅር ሽውታ እንዳይነካት ፈርተው
የርሷ ቤተሰቦች ቢያውሏት አብተው
እርሱን አጥመንምኖ ናፍቆቷ እየነቃ
በልክ የለሽ ፍቅር ቀይስየው ተጠቃ
ወቃ አክለፈለፈው፣ ዘርሮ አሸነፈው
አልቻል አለናም መጅኑን ሆኖ አረፈው
አፈቀርኩ አትበል መጅኑኑን ሳትመስል
እሷን ሲል ያበደ በሷው እሷኑ ሲል

መጅኑን ነህ መባሉን ሳይጠላ ወደደው
በስሟ ስለሆን ለለይላ ሆነና
በለይላ ነውና አፍቃሪው ያበደው

ከሃሳቡ ባህር ሲያሰጥም ሲያዋኛት
ከባህሩ ፈልቃ ወደ ገሃድ ዘልቃ
አንድ ለት አገኛት፣

አይን ላይን ፈዘዙ
ሰውኛ አንደበትን ትተው ከነ ጓዙ
በልብኛ ቋንቋ መነጋገር ያዙ
በሽምጠ ሃሳብ በልብኛ ሰጋር እርቀው ተጓዙ፣
ታዲያ የርሱ ለይላ
ከመሄዷ በፊት ፣ፈገግ ልበል ብላ
ክምችች ኮከብ ጥርሷን ከፊል ብትገልጠው
እብደትን በብደቱ እብድ ሆኖ በለጠው

ላትቀመጥ ቆማ፣ አይኗን አሳየችው
በጉልበቱ ገብታ አብረከረከችው

መባዘኑን ያዩ ባልጀራዎቹ
ይሰማ መስሏቸው፣
እርሳት ! በቃ ተዋት! ሲሉ እየሞገቱ
ሊያስተውት ከጅለው ፣ወቀሱት በብርቱ
ጆሮ ዳባ አላቸው
በርሷ የመጣበት ነውና ጠላቱ
አዎን ላፈቀረ ፣
የለይላ ለሆነች እስትንፋስ ህይወቱ
በለይላ ለሞላ ቀንና ሌሊቱ
የለይላን እንጂ የሌላን ከንችሮ
ስለ ለይላ ሚያልም ከሌላው ደንቁሮ
በለይላ ላበደ ለይላን ብቻ አፍቅሮ
እርሳት ተዋት ስትል አትንካ አትውቀሰው
በርሷ የመጣ ነው ጠላቱ ለዚህ ሰው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በ ሰኢድ አህመድ

@maraki_layrics
186 viewsedited  12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ