መኪናዋን አንቀሳቀሰችና ወደ መንገድ አስገባችው..በዝግታ መንዳት ጀመረች.. በእስፖኪዬና ወደኃላ ተመለከተች …አዎ እነሱም እንደእሷ ነው ያደረጉት …እየተከተሏት ነው፡፡ ‹‹ይሄውልህ አቶ ሄኖክ በደንብ ስማኝ ..በሚቀጥለው መጠመዘዣ ታጥፈው ወደኃላ ካልተመለሱ ለፖሊስ ደውዬ አሳስራቸዋለው፡›› ‹‹ተይ እንጂ… ምንን መሰለሽ?…..››አላስጨረሰችውም ስልኳን ጠረቀመችው፡፡. ወዲያው መልሶ ደወለላት.. .ዘጋችበትና አንድ ደህንነት የሚሰራ ባለስልጣን ወዳጆን ስልክ ከስልኳ ውስጥ ፈለገችና ዝግጁ ሆና መጠባበቅ ጀመረች፡፡ መታጠፊያውን አልፋ ነዳች ...ከኃላ ያሉት አጃቢዎቾ ምን እንደሚያደርጉ በጉጉት እና በስጋት እየተጠባበቀች ነው ‹‹ወይ እግዜር ይሰጣችሁ›አለች.ደስ ያላት እንደፈለገችው ባለችው መታጠፊያ ታጥፈው ወደኃላ ስለተመለሱ ነው.፡፡፡ ይቀጥላል.... ሀሳብ አስተያየታችሁን @itsmezeeddr አድርሱኝ ቶሎ ቶሎ እንዲለቀቅ እንዳይረሳ 387 viewsጌሰም, 20:50