Get Mystery Box with random crypto!

MAJIF የሙስሊም ወጣቶች ማህበር

የቴሌግራም ቻናል አርማ majif1 — MAJIF የሙስሊም ወጣቶች ማህበር M
የቴሌግራም ቻናል አርማ majif1 — MAJIF የሙስሊም ወጣቶች ማህበር
የሰርጥ አድራሻ: @majif1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 212

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-08-06 12:36:13 «የዐሹራእን ፆም የተመለከቱ የተወሰኑ ማስታዎሻዎች

የዐሹራእ ፆም የሚባለው እንደ ሒጅራ አቆጣጣር የመጀመሪያው የሙሐረም ወር በገባ በአስረኛው ቀን የሚፆም ፆም ነው።
ይህ ፆም እጅግ ከተጠኑ የሱና ፆሞች መካከል ከዋናዎቹ ነው።

وعن أبي قتادة -رضي الله عنه-، أنّ النّبي -صلّى الله عليه وسلّم- قال:
( صيامُ يومِ عاشوراء، أحتسب على اللَّه أنْ يُكَفِّرَ السّنة التي قبله ).
[أخرجه مسلم]

ከአቡ ቀታዳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዙ ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም)
"የዓሹራእ ቀን ፆም ከሱ በፊት የነበረውን ዓመት ወንጀል ያስምራል ብዬ በአላህ ላይ ተስፋ አደርጋለሁ" አሉ።

【ሙስሊም ዘግበውታል】

ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ)
ሰለ ዐሹራእ ፆም ተጠይቀው እንዲህ አሉ :-
" ነብዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሌሎች ቀኖች አሰበልጠው የሚፆሙበትን ቀን ሲጠባበቁ ከዚህ ቀን ውጪ አላውቅም (የዐሹራእን ቀን ማለቱ ነው።) ወርን ሲጠባበቁ አላየሁም የዚህን ወር ያክል (የረመዳን ወር ማለቱ ነው።)
【ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል】

የዐሹራእ ቀን የሚባለው የሙሐረም 10 ኛው ቀን ነው።
የሙሐረምን 10 ኛውን ቀን በፆም ማሳለፍ ከላይ በሐዲሡ ላይ እንዳየነው ያለፈውን የአንድ አመት ወንጅል ያስምራል

ለሙስሊሞች እሄን ቀን በመፆም እራሳቸውን፣ልጆቻቸውን፣ቤተሰቦቻቸውንና ማሀበረሰባቸውን ሊያነሳሱ ይገባቸዋል።

ማሳሰቢያ:- ያለፈውን የአመት ወንጀል ያስምራል ማለት ትንንሹን ወንጀል ነው እንጅ ትልልቁን ሀጢአት አይደለም ትልቅ ወንጀል ዝሙት፣ህሜት፣ነገረኝነት፣ሪባ እና መሰል ትልልቅ ወንጀሎች መስፈርቱን ያሟላ እራሱን የቻለ ተውበት ያስፈልጋቸዋል።

በዚህ ቀን ወደአላህ ልንመለስ ካለፈው ወንጀላችን በአጠቃላይ ከትልቁም ከትንሹም በመፀፀት እውንተኛ ተውበትን ልንቶብት ይገባል። ተውበትን አላህ በማንኛውም ጊዜ ቢቀበልም በእንደዚህ ብልጫ ባላቸው ጊዜዎች ከሌላው በተለዬ ጊዜ ይቀበላል። በተለይ እኛ እንደሂጅራ አቆጣጠር አድስ አመትን እየጀመርን ስለሆነ ካለፈው ጥፋታችን በመመለስ በተረፈው በመስተካከል ወደአላህ ልንመለስ ይገባናል።

የዐሹራእ ፆም ምክኒያት:-

የዐሹራእን ቀን መፆም ሱና ሁኖ የተደነገገው አሏህ ሙሳንና ህዝቦቾዎን ከፊርዐውን ሰላም ያወጣበት ቀን እንዲሁም ፊርዐውንና ሰራዊቱን ያጠፋበት ቀን ስለሆነ አላህን ለማመስገን ነው።
ለዚህም ተብሉ ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም) ይህን ቀን ፁመውታል አይሁዶችም ሙሳን ተከትለው ፁመውታል።እኛ ሙስሊሞች ሙሳን በመከተልና በሙሳ ሰላም መውጣት በጠላታቸው መጥፋት በመደሰት ከአይሁዶች የበለጠ የተገባን ነን

ከላይ የጠቀስኩት የዐሹራእ ፆም ምክንያት በዚህ ሐዲሥ ተገልፇል:-

عن ابن عباس ((قَدِمَ النَّبِيُّ -صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ- المَدِينَةَ فَرَأَى الْيَهُودَ تَصُومُ يَوْمَ عَاشُورَاءَ فَقَالَ مَا هَذَا؟ قَالُوا: هَذَا يَوْمٌ صَالِحٌ، هَذَا يَوْمٌ نَجَّى اللَّهُ بَنِي إِسْرَائِيلَ مِنْ عَدُوِّهِمْ فَصَامَهُ مُوسَى، قَالَ فَأَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى مِنْكُمْ فَصَامَهُ وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ)). 【صحيح البخاري】

ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ:–
"ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና በገቡ ጊዜ አይሁዶች የዐሹራእን ቀን ሲፆሙ አዩዋቸው ነቢዩም (ለአይሁዶች) "ይህ (የምትፆሙት) ምንድነው?" አሉዋቸው ይህ ምርጥ ቀን ነው ይህ ቀን አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው ሰላም ያወጣበት ቀን ነው። ስለዚህ ሙሳ ፆሞታል። አሉ ነቢዩም "እኔ ለሙሳ ከናንተ የበለጠ የቀረብኩኝ(የተገባሁኝ) ነኝ ብለው ፆሙት እንዲፆምም አዘዙ።"
【ቡኻሪ ዘግበውታል】

ከአስረኛው ቀን በስተፊት ያለውን ማለት የዘጠነኛውን ቀን አብሮ መፆም ይወደዳል

ኢብኑ ዐባስ(ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ ይላሉ:-
"ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዐሹራእን በፆሞና እንዲፆምም ባዘዙ ጊዜ (ሱሐቦች) የአላህ መልእክተኛ ሆይ እርሱኮ አይሆዶችና ነሷራዎች የሚያከብሮት ቀን ነው አሏቸው። ነቢዩም (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) «አሏህ ካለ በቀጣይ አመት የዘጠነኛውን ቀን እንፆማለን» አሉ (ኢብኑ ዐባስ) "የቀጣዩ አመት አልመጣም ነቢዩ(አለሂሶላቱ ወሰላም) የሞቱ ቢሆን እንጅ" አለ
【ሙስሊም ዘግበውታል】
ስለዚህ ለዚህ ሐዲሥ ሲባል ዘጠነኛውን ቀን ከአስረኛው ጋር አብሮ መፆም ይወደዳል

« አስረኛውን ብቻ በፆም መለየት ከአይሁድ ጋር እንዳይመሳሰል ከሙሐረም ዘጠኝና አስርን አብሮ መፆምን ብዙ ዐሊሞች ይወደዳል ብለዋል (ከነርሱም መካከል) ኢማሙ ማሊክ፣ኢማሙ ሻፊዒይና ኢማሙ አሕመድ»

ምንጭ【ሶሒሁ ፊቂሂ ሱናህ (2/121)】

ከላይ ያሳለፍነው ሐዲሥ ከከሀዲዎች ጋር መመሳሰል በሸሪዓችን ክልክል እንደሆነ መረጃ ነው።ሸሪዓ እንድህ በዒባዳቸው እንኳ እንዳንመሳሰል ይከለክለናል ዛሬ የሚያሳዝነው ብዙው ወጣት በሚሰሩት ሀራም እና ፀያፍ ተግባራቸው ሳይቀር ይከተላቸዋል ውርደት ማለት እሄነው። አላህ ከውርደት ይጠብቀን

ቀደምቶቻችን የዐሹራእን ፆም በአስቸጋሪ ሆኔታ እንኳ ቢሆኑም ይፆሙት ነበር

ኢማም ዙህርይ ሙሳፊር(መንገደኛ) ሁነው ሳለ የዓሹራን ፆም ፆሙ
ለርሳቸውም "አንቱ በመንገድ ላይ ስትሆኑ ከረመዳን ፆም እያፈጠርኩ ለምን (በመንገድ ላይ ስትሆኑ) ዓሹራን ትፆማለሁ" ተባላቸው

"ረመዷን በሌላ ቀን (የቀዷ ማውጫ) ግዜ አለው ዓሹራእ ግን ያልፋል (የማካካሻ ቀን የለውም)
በማለት መለሱ

【ሲየሩ አዕላሚ ኑበላእ (5/342)】

በዚህ የዐሹራ ቀን ሁለት ቡድኖች ተሳስተው ጠመዋል

የመጀመሪያዎቹ:-
ዓሹራእን ልክ እንደ ዒድ ወን አድርጎ በመያዝ በዚህ ቀን አድስ ልብስ ይልብሳሉ የተለየ ምግብ ያዘጋጃሉ እንድሁም በመኳኳልና በመቀባባት ይበጃጃሉ አንዳንዶቹም መውሊድ በማድረግ ይደግሳሉ ይህ ሁሉ ረሱል(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንድንሰራው ያላዘዙን ጥመትና ቢድዓ ነው። ከእንድህ አይነት ጥፋት እኛም ቤተሰቦቻችንም ልንርቅ ይገባናል።

ሁለተኞቹ:-
አንጃዎች ደግሞ እሄን ቀን ሑሰይን ኢብኑ ዐሊይ(ረዲዬሏሁ ዐንሁ) የተገደለበት ቀን ነው በማለት የአዘን እና የለቅሶ ቀን አደረጉት በዚህቀን አዝነው ተግዘው ሲያለቅሱ ሌሎችም የጃሂልያ ተግባር ሲያደርጉ ይውላሉ ይህም በሸሪዓ ያልተደነገገ ጥመት ነው።

አሏህ በእነዚህ ሁለት የጠፉ አንጃዎች መካከል አህሉሱኖችን ለቀጥተኛው መንገድ መራቸው እሄንቀን ረሱል (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዳዘዟቸው በመፆም እና ሌሎችንም የተደነገጉ ዒባዳዎች በማድረግ ያሳልፉታል

የዐሹራእ ፆም ትሩፋቱና ምክኒያቱ እሄን ይመስላል ወሏሁ አዕለም


ዋናዉ ፃሙ የሚጀምረው ሰኞ ሲሆን
ዘጠነኛዉ ደግሞ እሁድ ነዉ።»

ኢብኑ ሙሐመድዘይን
48 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 18:28:02 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ ዛሬ አንድ ሰው ለመጠየቅ ወደ አለርት ሆስፒታል ጎራ አልኩና በድንገተኛ ክፍል ውስጥ ያየውትን ላጋራቹ ወደድኩኝ..... ሰዎች አላህ በኛ ላይ የዋለውን ፀጋ አንርሳ ከትላልቅ ፀጋዎቹ ዋንኛው ደግሞ ኣፊያ ነው...ሁሌም አመስጋኝ ባሪያ እንሁን እንደዚህ አይነት ልብ ሚያረቁ ቦታዎችን ለልባችን ድርቀት ማከሚያ እናርጋቸው..
ወንድማቹ ሰዒድ ጀማሌ
80 viewsedited  15:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 18:24:23
80 views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 16:39:21 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته አልሐምዱሊላህ የዛሬው python programming ትምህርታችን በጥሩ ሁኔታ ተካሂዷል ። በአላህ ፍቃድ ነገ web development ትምህርታችን ይቀጥላል ። ሆኖም #projector ባለማግኘታችን ምክንያት ያሰብነውን ያህል መሄድ አልቻልንም ። እስቲ ማግኘት የምትችሉ "አለሁ" በሉን ባረከላሁፊኩም ። በኪራይም ማግኘት ከተቻለ ይቻላል…
62 views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 20:06:30 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
አልሐምዱሊላህ የዛሬው python programming ትምህርታችን በጥሩ ሁኔታ ተካሂዷል ። በአላህ ፍቃድ ነገ web development ትምህርታችን ይቀጥላል ። ሆኖም #projector ባለማግኘታችን ምክንያት ያሰብነውን ያህል መሄድ አልቻልንም ። እስቲ ማግኘት የምትችሉ "አለሁ" በሉን ባረከላሁፊኩም ። በኪራይም ማግኘት ከተቻለ ይቻላል ።

ሌላው Laptop ያላችሁ ይዛችሁ መምጣት እንዳትረሱ
41 viewsedited  17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 15:02:56 Laptop የምትጠቀሙ ይህንን ፋይል download አድርጉ
77 viewsedited  12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 15:00:33 ባለፈው በተነጋገርነው መሰረት በሚመጣው ቅዳሜ የ python programming እንዲሁም እሁድ የ website development ኮርስ እንጀምራለን።
ቦታ:- ነፍራ ት/ቤት
ሰዓት :- 3:30-5:30
ማንኛውም የማጂፍ አባል መሳተፍ ይችላል ።
79 viewsedited  12:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 17:42:12
76 views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ