Get Mystery Box with random crypto!

Lovedface የተወደደ መልክ

የቴሌግራም ቻናል አርማ lovedface — Lovedface የተወደደ መልክ L
የቴሌግራም ቻናል አርማ lovedface — Lovedface የተወደደ መልክ
የሰርጥ አድራሻ: @lovedface
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.08K
የሰርጥ መግለጫ

ጌታን በማወቅና በክርስቶስ ፍቅር የሆነ ጥልቅ የመንፈስ ቅዱስ ህብረት
@Lovedface @emanuellf

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-27 10:40:04 የመዳን ተሸካሚዎች

RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic)

Wednesday July 27th, 2022
(ረቡዕ - ሐምለ 20 - 2014)

════════
የብሩክ እግዚአብሔርንም ክብር እንደሚገልጥ ለእኔ አደራ እንደ ተሰጠኝ ወንጌል (1ኛ ጢሞቴዎስ 1፡11)

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
እንደ ክርስቲያኖች የማስታረቅ አገልግሎት አለን። የእኛ የወንጌል ስራ አለማችንን መድረስና ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ማስታረቅ ነው። ይህን መፈፀም አለብን። በኢየሱስ ክርስቶስ ያመንን እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ወዳለ ህብረት እንድንመጣ ሆኗል (1ኛ ዮሐንስ 1፡3)። ነገር ግን አለም በጠቅላላው ወደዚህ ህብረት ገና አልመጣም። እነርሱን ማምጣት የእኛ ኃላፊነት ነው።

ኢየሱስ በማርቆስ 16፡15 ላይ እንዲህ አለ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።” ይህ ትዕዛዝ የተሰጠው ለእኛ ለደቀ መዝሙሮቹ እንጂ ለመላዕክት አልነበረም። ሰዎችን ወደ ክርስቶስ እንዲመጡ እንዲያደርጉ እግዚአብሔር መላዕክትን እንዲልክ የሚፀልዩ ሰዎች አሉ። ነገር ግን ያ የመላዕክት ስራ አይደለም። የእነርሱ ስራ እኛ ወንጌልን እንድናገለግላቸው ሰዎችን ከእኛ ጋር እንዲገናኙ ማድረግ ነው።

እኛ የመዳን መልዕክት ተሸካሚዎች ነን። ሰዎችን በክርስቶስ ኢየሱስ ወዳለ ደህንነት የምንመራው እኛ ነን። ምናልባት የሆነ ሰው እንዲህ ሊል ይችላል “ነገር ግን በራዕይ 14፡6-7 የዘላለም ወንጌልን ሊሰብክ ስላለው መልዓክ ተነግሮናል፤ ‘በምድርም ለሚኖሩ ለሕዝብም ለነገድም ለቋንቋም ለወገንም ሁሉ ይሰብክ ዘንድ የዘላለም ወንጌል ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ መካከል ሲበር አየሁ፤ በታላቅ ድምፅም። የፍርዱ ሰዓት ደርሶአልና እግዚአብሔርን ፍሩ ክብርንም ስጡት፤ ሰማይንና ምድርንም ባሕርንም የውኃንም ምንጮች ለሠራው ስገዱለት አለ።’”

የዚህ መልአክ መልዕክት የመዳን መልዕክት ሳይሆን ቁጥር 7 ላይ ባለው የተሰመረበት ጥቅስ ላይ እንደሚታየው የፍርድ ነበር። የደህንነት ወንጌልን መስበክ በግልፅ ለእኛ የተመደበ ተግባር ነው። በሐዋርያት ስራ 10 ላይ መጽሐፍ ቅዱስ አንድ መልአክ ስሙ ቆርኔሌዎስ ወደ ተባለ የሮም ወታደር እንዴት እንደተላከ ይነግረናል (ሐዋርያት ስራ 10፡1-3)። ነገር ግን መልዓኩ ወንጌልን ለቆርኔሌዎስ አልሰበከለትም።በዚያ ፈንታ መልአኩ ከስምዖን ጴጥሮስ ጋር እንዲገናኝ አደረገው። እርሱም መጥቶ ለቆርኔሌዎስና ለቤተሰዉ ሰበከ፤ እነርሱም ደህንነትን ተቀበሉ።

እኛ እስከ አለም ጥግ ድረስ የመዳን መልዕክትን ተሸካሚ መሆናችን እንዴት የከበረ ሃላፊነት ነው! እግዚአብሔር ይባረክ! በዚያ ደስተኛ መሆን አለባችሁ። የህይወታችሁ ስራ አድርጉት። በወንጌል ለማገልገል፣ የእርሱን ጽድቅ ለማሳወቅ እና መንግስቱን በምድርና በሰዎች ልብ ውስጥ ለመመስረት እድል ተሰጥቷችኋል።

ጸሎት
━━━━━━━━
ውድ ጌታ ሆይ፤ የመዳን መልዕክትን ተሸካሚ ለመሆን ስለሰጠኸኝ እድል አመሰግንሃለሁ። ሰዎችን ወደ ጽድቅ ለመመለስ ከጨለማ ወደ ብርሃን እና ከሰይጣን ስልጣን ወደ እግዚአብሔር ዘወር እንዲሉ ለማድረግ የሚያስፈልገውን ፀጋ ስለሰጠኸኝ አመሰግንሃለሁ። የክርስቶስና የወንጌል አምባሳደር በመሆን አገልግሎቴን ዛሬ እፈፅማለሁ። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
የማርቆስ ወንጌል 16:15-16;
ትንቢተ ዳንኤል 12:3;
2ኛ ቆሮንጦስ 5:18-19;
የማቴዎስ ወንጌል 28:19
━━━━━//━━━━
136 views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 09:00:19
162 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 09:00:19 የእግዚአብሔር ፍቅር መገለጥ

RHAPSODY OF REALITIES
በድምፅ - ራፕሶዲ ኦፍ ሪያሊቲስ

Tuesday July 26th, 2022
(ማክሰኞ - ሐምሌ 19 - 2014)
147 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 09:00:19 የእግዚአብሔር ፍቅር መገለጥ

RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic)

Tuesday July 26th, 2022
(ማክሰኞ - ሐምሌ 19 - 2014)

════════
ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና (1ኛ ዮሐንስ 4፡8)

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ፍቅር ነው ይላል! ይህ ቀላልአረፍተ ነገር ቢሆንም እጅግ ጥልቅ ነው። ነገር ግን ትርጉሙ ምንድነው? እግዚአብሔር ፍቅር ከሆነ እርሱ ምንድነው የሚመስለው? ወይም ደግሞ ፍቅር ምንድነው የሚመስለው? ለትውልዶችና በሺህ ለሚቆጠሩ አመታት የዚህ መረዳት መገለጥ ለብዙ ሰዎች ግልፅ ያልሆነ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔርን ያየው አንድም ሰው አልነበረም (1ኛ ዮሐንስ 4፡12)። ስለዚህም እግዚአብሔር ማን እንደነበረና ፍቅር ምን እንደሆነ የነበራቸው መረዳት ከእውነቱ የራቀ ምናባዊ እይታ ብቻ ነበር።

ነገር ግን “እኔን ያየ አብን አይቶአል…” ብሎ የተናገረው ኢየሱስ መጣ (ዮሐንስ 14፡9)። ኢየሱስ በስጋ የተገለጠ አምላክ ነበር (1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16)። በገሊላ መንገዶችም በሚመላለስበት ጊዜ እርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር አካላዊ መልክ፤ መገለጥ ነበር። 1ኛ ዮሐንስ 4፡9 እንዲህ ይላል “በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።” ኢየሱስ ለእኛ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፍቅር ነበር። እርሱ የተገለጠ ፍቅር ነበር። ይህ ነገር እኔ በህይወቴ ዘመን ሁሉ ካገኘኋቸው እጅግ አስደናቂ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው። ይህም ወደ እኔ የመጣውም በራዕይ መልክ ነበር። ፍቅር እንደ ሰው ሆኖ ከፊት ለፊቴ ሲራመድ አየሁኝ። ያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር! በእውነትም ኢየሱስ ፍፁም የሆነ የፍቅር ምንነት መግለጫ ነው! ከዚህ በተጨማሪስ?

መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል “ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ። ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።” (1ኛ ዮሐንስ 4፡7-8 ኤንኬጄቪ ትርጉም)። ይህ ማለት የእግዚአብሔርን ፍቅር ለማወቃችን ማረጋገጫው ያን ፍቅር የምናሳይበት መንገድ ነው። ምክንያቱም ዛሬ እኛ የእርሱ ባህሪ፣ ችሎታና ማንነት መገለጥ ነን። እናንተ የእግዚአብሔር ፍቅር ማስረጃ ናችሁ።

እስካላሳያችሁት ድረስ የእግዚአብሔርን ፍቅር አውቀዋለሁ ማለት አትችሉም። የእሱ ፍቅር በእናንተ ውስጥ መታየት አለበት። ይህም መጽሐፍ ቅዱስ በኤፌሶን 3፡10 ላይ እንዲህ ሲል የሚናገረውን ያስታውሳል“ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ፤” የእግዚአብሔር እቅድና ህልም እርሱን፣ የእርሱን ፍቅር፣ መለኮታዊ ልቀትና ጥበብ በቤተ ክርስቲያን በኩል መግለጥ ነው። ይህም በእናንተ ውስጥ እየተከናወነ ነው። ሃሌ ሉያ!

የእምነት አዋጅ
━━━━━━━━
በውስጤ በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የእግዚአብሔር ፍቅር በልቤ ፈስሷል። የእርሱ ፍቅር ማስረጃ፣ የባህሪው፣ የችሎታውና የማንነቱ መገለጥ እኔ ስለሆንኩኝ ፍቅሩ በየእለቱ በእኔ ውስጥ ይገለጣል፣ በኢየሱስ ስም። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
ሮሜ 5:5;
1 የዮሐንስ ወንጌል 4:12-13
━━━━━//━━━━
150 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 10:02:03
በቅዱሳን መካከል ርስትን ሊያካፍላችሁ የሚችለውን የፀጋ ቃል ዛሬ ተቀበሉ።

ሰኞ ከ11:00 - 12:00, እና ከ12:00 - 1:00 (Foundation ትምህርት)
ቅዳሜ ከ11:00 - 12:00 (የመንፈስና የቃል ህብረት)
ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊትለፊት በሃቅ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢ.ቁ 45
+251912606346
179 views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 10:00:04
158 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 10:00:04 በልሳን ለምን እንናገራለን?

RHAPSODY OF REALITIES
በድምፅ - ራፕሶዲ ኦፍ ሪያሊቲስ

Monday July 25th, 2022
(ሰኞ - ሐምሌ 18 - 2014)
133 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 10:00:04 በልሳን ለምን እንናገራለን?

RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic)

Monday July 25th, 2022
(ሰኞ - ሐምሌ 18 - 2014)

════════
በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ማኅበሩን ያንጻል (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡4)

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
ኢየሱስ በሐዋሪያት ስራ 1፡8 ላይ እንዳለው መንፈስ ቅዱስን ስትቀበሉ በእናንተ ውስጥ እንዲኖር የእግዚአብሔርን ኃይል ተቀብላችኋል። ይህ ኃይል የሚንቀሳቀሰው ወይም የሚሰራው በልሳን ስትጸልዩ ነው። በመክፈቻ ጥቅሳችን “ያንጻል” የሚለውን ቃል በግሪኩ “ኦይኮዶምዮ” ይለዋል፣ ያ ማለት መገንባት ወይም መስራት፣ ባትሪያችሁን በኃይል እንደምትሞሉት ያደፋፍራችኋል ወይም ይሞላችኋል።

ስለዚህ በልሳን የሚናገር ልክ እንደ ህንጻ ራሱን እንደሚገነባ ያ ጥቅስ ይነግረናል፤ ራሱን ያደፋፍራል፤ ልክ እንደ ባትሪ ራሱን በኃይል ይሞላል። በልሳን በመናገር ጊዜያችሁን ስትወስዱ፣ መንፈሳችሁን ትገነባላችሁ። ”እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥” (ይሁዳ 1፡20)። በክርስትና ህይወታችሁ ደካማ ከሆናችሁ፣ በልሳን ስትናገሩ፣ በእናንተ ውስጥ ዝም ያለው የእግዚአብሔር ኃይል ይነሳሳል፤ የእግዚአብሔርን ስራዎች ለመስራት ብርቱ ትሆናላችሁ። በልሳን መናገር ለፍርሃትና ለአይናፋርነት መድሃኒት ነው።

እንደ ክርስቲያን፣ እግዚአብሔር የፍርሃትን መንፈስ ሳይሆን የኃይል፣ የፍቅርና ራስን የመግዛት መንፈስ እንደሰጣችሁ ማወቅ አለባችሁ። (2ኛ ጢሞቴዎስ 1፡7)። በልሳን በመጸለይ ጊዜን በመውሰድ በውስጣችሁ ያለውን ኃይል አነሳሱ፤ ይህንን በየቀኑ ሁልጊዜ አድርጉት። የውስጥ ሰውነታችሁ እጅግ ጠንካራ ሆኖ ይገነባል፤ በዘላቂነት በጠላቶቻችሁ ላይ የበላይ ሆናችሁ ትጓዛላችሁ።

በልሳን መናገር ወንጌልን ለመስበክ ብቁ ያደርጋችኋል። አንድ የዘጠኝ አመት ወንድ ልጅ ለጓደኞቹ ወንጌልን ለመመስከር ያፍርና ያልቻለ የነበረውን ምስክርነት ሰምቻለሁ። በልሳን መናገር ከጀመረ ጊዜ በኋላ፣ በራሱ የሚተማመን ሆነ እናም ፈሪ የነበረው ልጅ በየቦታው ደፋር የወንጌል ሰባኪ ሆነ።ለእናንተ የመለኮታዊ ጥበብን የሚያቀርበውን የእግዚአብሔርን ምስጢር እንደምትናገሩ በማወቅ በየቀኑ በልሳን በመናገር ጊዜ ስትወስዱ፣ እግዚአብሔር በህይወታችሁ ዛሬ የሚሰራው ገደብ የለውም።

በተጨማሪ በልሳን መናገር “ፈጣን የሆነ ኃይል” ያቀርብላችኋል፤ እናም መንፈሳችሁ ለመለኮታዊ ምልክቶች ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ ያደርጋል። በልሳን መናገር ታላቅ በረከት ነው። ስለዚህ ነገር የበለጠ “የልሳን ኃይል” ከሚለው መጽሃፋችን መማር ትችላላችሁ። አግኙት በጥንቃቄ አጥኑት፤ መንፈሳችሁን በልሳን በመናገር ለሚገኝ ታላቅ ትሩፋት “ግሎሶላሊያ” (በግሪክ) እድል ስጡት።

ጸሎት
━━━━━━━━
ውድ አባት ሆይ፣ በልሳን በመናገር ስለሚገኝ የሚያነቃቃ፣ የሚያነሳሳ፣ መንፈስን የሚያድስ፣ ኃይል የሚሰጥ እና የሚያንጽ ልምምድ አመሰግንሃለሁ። እኔን በሚመለከቱ በነገሮች ሁሉ ለውጥ አለ፤ መንፈሴ ለስኬት፣ ለልህቀት፣ ለብልጽግና እና ለድል ተዘጋጅቷል። አሁን እንኳ በልሳን ስናገር ከውስጤ የህይወት ውሃ ምንጭ ይፈልቃል፡፡ የማዳን፣ የፈውስ፣ የብርታት ቃል ከእኔ ወደ አለሜ ይፈሳል፣ በኢየሱስ ስም። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
ትንቢተ ኢሳያስ 49:15-16;
1 የዮሐንስ ወንጌል 3:1;
1 የዮሐንስ ወንጌል 4:16
━━━━━//━━━━
153 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 09:45:01 በግላችሁ ይወዳችኋል

RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic)

Sunday July 24th, 2022
(እሁድ - ሐምሌ 17 - 2014)

════════
እግዚአብሔርም ከሩቅ ተገለጠልኝ እንዲህም አለኝ። በዘላለም ፍቅር ወድጄሻለሁ፤ ስለዚህ በቸርነት ሳብሁሽ (ኤርምያስ 31፡3)

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
ከሆነ ጊዜ በፊት አንድ ምስክርነት እየሰማሁ ነበር፣ እናም የምትመሰክረው ሴት እንዲህ አለች፤ “እግዚአብሔር ይሄን ያክል እንደሚወደኝ አላውቅም ነበር፡፡” ይህ ንግግር በጥልቀት ነካኝ። እግዚአብሔር እንደሚወዳት አወቀች ነገሯም ሁሉ ተቀየረላት። እግዚአብሔር እንደሚወዳችሁ በግላችሁ መገንዘብ በህይወታችሁ ማግኘት ከሚገባችሁ ታላቅ ግኝቶች አንዱ ነው።

ዕብራውያን 13፡5 እንዲህ ይላል፤ “…እርሱ ራሱ አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤” ይህ ማለት ከእርሱ ርቃችሁ ቢሆን እንኳ፣ እንደማትፈልጉት እስክታረጋግጡለት ድረስ ከኋላችሁ ይከተላችኋል። ነገር ግን ሁል ጊዜ ይፈልጋችኋል፤ እናም ሁል ጊዜ ይወዳችኋል። በእናንተ ለምን ተስፋ አይቆርጥም? ሁል ጊዜ ለምን ይፈልጋችኋል? ወደፊትም ለምን ይፈልጋችኋል? ምክንያቱም በየግላችሁ ይወዳችኋል። በእውነትም ያንን ያደርጋል። በምድር ላይ ያለ አንድ ሰው እናንተ ብቻ ብትሆኑ እንኳ ኢየሱስ መጥቶ ለእናንተ ይሞትላችኋል።

እናንተን ሲፈጥራችሁ ልክ እርሱን እንድትመስሉና እንደ እርሱ እንድትሆኑ አድርጎ ፈጥሯችኋል። በእናንተ ውስጥ ራሱን ይመለከታል። ስታጠፉ የሚያስበው እንዴት መቅጣት እንዳለበት አይደለም፣ ይልቁን ሊረዳችሁና እንድትሆኑ የሚፈልገውን እንድትሆኑ ይፈልጋል። ቃሉን ከሰማችሁ እና ከተቀበላችሁ የተሻለ እንደምትሆኑ ያውቃል፤ ስለዚህ እናንተን ለማረም፣ ለመምራትና ፍጹም ለማድረግ ሁል ጊዜ ቃሉን ያመጣላችኋል። ያለ ምንም ይወዳችኋል።

በቤተሰቦቻችሁ የሚጠሏችሁ የሆኑ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። አንዳንድ እናንተን የማይወዱ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን እሱ ግድ አይልም። በእውነት ግድ የሚለው አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው፤ እናም እሱ በፍቅር ይወዳችኋል። ይሄ ከአለም ሁሉ የሚበልጥ ይሁንባችሁ።

ጸሎት
━━━━━━━━
የምታፈቅረኝ አባት ሆይ፣ ገደብ ለሌለው ፍቅርህ፣ በእኔ ላይ ስላፈሰስከው ፍቅር አመሰግንሃለሁ። ለአንተ እንዲህ ልዩና ዋጋ ያለኝ መሆኔን ማወቅ በጣም የሚያስደስት ነው። በየቀኑ በማይጥለው ፍቅርህ መረዳት ውስጥ እመላለሳለሁ። ፍቅርህን ዛሬ ለአለሜ እገለጣለሁ አበራለሁም፣ በኢየሱስ ስም። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
ትንቢተ ኢሳያስ 49:15-16;
1 የዮሐንስ ወንጌል 3:1;
1 የዮሐንስ ወንጌል 4:16
━━━━━//━━━━
203 views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 10:25:22
የመንፈስ ቅዱስን ጥልቅ ህብረትና የህያው የቃሉን መገለጥ በመንፈሳችሁ ተቀበሉ። በእውነትም ህይወታችሁ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።

ቅዳሜ ከ11:00 - 12:00
ሰኞ ከ12:00 - 1:00
ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊትለፊት በሃቅ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢ.ቁ 45
+251912606346
199 views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ