2022-08-27 08:56:11
ሦስታችን አንድ ነን!
በ11ኛው ክፍለ ዘመን ከሦስቱ አባቶች ዘንድ ማነው የሚበልጥ የሚል ጠብ ተነሳ። እኒህ ሦስቱ የተባሉት ፓትርያርኮችና ቅዱሳን ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ናቸው። በቤዛንታይን ማኅበረሰብ ዘንድ በዚህ ጠብ የተነሳ መከፋፈልና መጎሳሰሞች ነገሱ፣ የቅዱሳኑን ትምህርት እየጠቀሱ ይበላሉ ጀመር። ክፍፍላቸውም የተለያዩ መልኮችን እየያዘ ለአራሚ እና ለመካሪ አስቸጋሪ ሆነ። ይኽም ወንድምን ከወንድም፣ ጎረቤትን ከጎረቤት ወዳጆችን ከወዳጆች እየለየ ክርስቲያኖችን የሚከፋፍል ሆነ....ይኽ አይነቱ ነገር ደግሞ የክርስትናን መመሪያ(The Christian Principles) ከሆኑት ሰላምና አንድነት ጋር ይጣረሳል።
በአንድ ወቅት በዘመኑ የነበረው አባ ማውሮፖስ ራእይን አየ...ሦስቱ ቅዱሳንም መጥተው እንዲህ ሲሉት ተመለከተ...
"ሦስታችን አንድ ነን፤ እንደምታዩትም ለፈጣሪ ቅርብ የሆንንና ምንም ሊለየንና ሊያጣላንም አይችልም...በመካከላችን አንደኛም ሁለተኛም የለም...እንግዲህ ተነስና በእኛ ላይ እንዳይከፋፈሉ የሚጣሉትን ንገራቸው። ምክንያቱም በሕይወትም በሞትም ለሰው ሁሉ ሰላምንና አንድነትን ለማምጣት እንጅ ሌላ ፍላጎት አልነበረንም።"
ይኽንንም ከሰሙ በኋላ ብዙዎች መንገዳቸውን ያስተካከሉ አሉ። በዚኽም በዚያ ዘመን የእኒህን ቅዱሳን መታሰቢያ(ዝክር) በአንድ ቀን እንዲውልና ሥዕላቸውም በአንድ እንዲሳል ተደረገ...የከበረች በረከታቸው ትርዳን፣ ትደርብንም!
ዘገየ ዘአስኩ
194 views05:56