2022-08-21 13:21:34
.
በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስም!! °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
መጽሐፍ ቅዱስ ስናገር ፦ " ...አንድ ጊዜ አንድ ሰው ወደ ኢየሱስ ቀረበና ተንበርክኮ፦ ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤ ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና።
ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው። ...ወደ ዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ። ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ። ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና፦
እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት። “
ኢየሱስም፦ ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።” አላቸው።
— ማቴዎስ 17፥14-20 ብዙዎቻችን በችግር ውስጥ ያለነው፤ በማጣት ውስጥ ያለነው፣ በህመም ውስጥ ያለነው፤ በእምነታችን ማነስ ምክንያት ነው። ምክንያቱም
ጌታ ኢየሱስ ስናገር ለሚያምን ጥቅት ይቻላል አላለም !! ያለው ለሚያምን ሁሉ ይቻላል... ነው። ሁሉ ውስጥ ጤንነት አለ፣ ሁሉ ውስጥ ገንዘብ አለ፣ ሁሉ ውስጥ ሰላም አለ፣ ሁሉ ውስጥ ሁሉም አለ። የእግዚአብሔር ቃል እራሱ እግዚአብሔር ነው። ቃሉን ስናምን የተነገረውን እግዚአብሔርን እናምናለን። ስለዚህ እምነት ማለት ስንታመም፤ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ "በርሱ ቁስል ተፈወስኩ" ቢለን ፈዉሳችንን በእምነት መቀበል መቻል ነው።
ምንም አይነት በሽታ ቢመጣ በርሱ ቁስል ተፈወስን የሚለውን ቃል አይሽርም። ምክንያቱም በርሱ ቁስል እኛ ተፈውሰናልና ምድር ላይ አዲስ ሀጢያት መጣ ብለን አንሰጋም፥ በየሚዲያው የምንሰማው አዲስ በሽታም አያሰጋንም። ክርስቶስ አንድ ጊዜ ለሁላችንም በመስቀል ላይ ተሰቅሏል። አሁን ዳግም ወደ ምድር መቶ መሞት አይጠበቅበትም። እየሱስ የሞተው ድሮ ለነበረው ሀጢያት ብቻ ሳይሆን አሁን እኛ እየሰራን ላለነው ሀጢያትም ጭምር ነው። ይሄንን ማመን ያለብክ እኛ ነን።
የእምነታችን መሰረት እየሱስ ክርቶስ ነው።
መጽሀፍ ሲናገር “ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤” ይላልና። (--1ኛ ቆሮንቶስ 15፥1) የቆምነው በክርስቶስ ላይ ነው “በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ። ” (—1ኛ ቆሮንቶስ 15፥2)
መጽሀፍ ቅዱስ የሕይወት እንጂ የሀይማኖት መመሪያ አይደለምና። “እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና (—2ኛ ቆሮ 5፥6-7 )መከራ፣ ድልም፣ መውደቅም፣ መነሳትም፣ በሆነ ጊዜ የምንመላለሰው በእምነት መሆን አለበት። ውጤቱ ስላማረ ብቻ አይደለም። ማመን ያለብን ነገር ግን፤ ሁኔታችን የሚስተካከለው ባመነው መጤን ወይም በክርስቶስ ላይ ባለን እምነት ልክ ነው። ለምሳሌ መጽሀፍ ቅዱስ ሲናገር፦ “ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።” ቢሎ በፊልጵስዩስ 4፥13 ይነግረናል። ይሄ ማለት፦ ሁል ጊዜ ፈተና ውስጥ ብትገባ የምታልፍበት መንገድ አስቸጋሪ ቢሆንም እንኳን ቃሉን ስታምን በክርስቶስ ላይ ያለህ እምነትህ፣ አቋምህ ፈጽሞ አይቀየርም። መጽሐፍ ቅዱስ ስናገር፦ “ነገር ግን፦ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤” (— 2ኛ ቆሮ 4፥13) የምናምነው ግን የምናየውን ሳይሆን የማይታየውን ነገር ግን በእምነት ዓለም ውስጥ ያለውን ነው።
የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ" የሚል የሁልጊዜም መልዕክተ ነው...!! (ወደ ቆላስይስ 3:16)' እወዳችኋለሁ። የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ዘራችሁን፣ ኑሮዋችሁን፣ ቤታችሁን፣ ዘመናችሁንና ትዳራችሁን ሁሉ ይባርክ።
#መልካምና_ያማረ_ቀን_ይሁንላችሁ
እግዚአብሔር ሀገራችን እትዮጵያን ሰላም ያድርግልን። ቸር ሰንብቱ።
join share follow & comment
ሕያው ቃል /Living Word/
https://telegram.me/Living_word_of_GOD
https://telegram.me/Living_word_of_GOD
https://telegram.me/Living_word_of_GOD join #በማድረግ፤
ይ ላ ሉን
እንዲሁም በአገልግሎታችን ላይ ጥያቄ ወይም ሀሳብ አስተያየት ካሎት፥ Contact Us፦ @Berhaneyesus or @LW_comment_Bot በመጫን ያድርሱን፡፡
1.2K viewsB𝕖𝕣𝕙𝕒𝕟𝕖 Y𝕖𝕤𝕦𝕤 (O𝕗𝕗𝕚𝕔𝕚𝕒𝕝), edited 10:21