በደቡብ ክልል ሃድያ ዞን በምሥራቅ ባድዋቾ ወረዳ እና ሾኔ ከተማ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ላለፉት ሦስት ወራት ደሞዝ ባለመግኘታችን ተቸገርን አሉ፡፡ ሠራተኞቹ በደሞዝ አጦት የተነሳ አንዳንዶቹ የሚበሉት በማጣት የቤት እቃዎቻቸውን እየሸጡ ፤ ከፊሎቹም ቤት ኪራይ መክፈል ባለመቻላቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመጠጋት መገደዳቸውን ገልጸዋል።ክፍያው ሊፈጸም ያልቻለው የቀድሞው የወረዳው አመራሮች የመንግሥት ሠራተኞችን የደሞዝ በጀት በዋስትና በማስያዝ የወሰዱሱት የአፈር ማዳበሪያ ዕዳ ባለመከፈሉ አሁን ላይ በዋስትና የተያዘው የደሞዝ በጀት ለአበዳሪው አካል ገቢ በመደረጉ ነው መባሉን ዶቼ ቬለ ዘግቧል፡፡ @Leyu_News @Leyu_News 2.1K views14:18