Get Mystery Box with random crypto!

ሁለቱ አስከሬን ተገኝቷል ለህንጻ ግንባታ የተቆፈረ አፈር ተንዶ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፋን ብስ | LEYU NEWS

ሁለቱ አስከሬን ተገኝቷል

ለህንጻ ግንባታ የተቆፈረ አፈር ተንዶ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፋን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታዉ መነን  ሰፈር እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ  ለህንጻ ግንባታ መሰረት የተቆፈረ አፈር ተንዶ የሁለት ሰራተኞች ሕይወት ማለፋን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቃል።

አደጋው በዛሬው ዕለት ከቀኑ 8:59 ላይ ልዩ ቦታው መነን ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መከሰቱን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

ለህንጻ ግንባታ ስራ የተቆፈረው አፈር ተንዶ በስራ ላይ የነበሩ ሁለት ሰራተኞች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን የአንደኛው አስከሬን አስቀድሞ ተገኝቷል።

በፍለጋ ላይ የነበረው ሁለተኛው አስከሬን የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን እንዲሁም ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር  ማውጣት መቻላቸውን ጠቁመዋል።በመዲናዋ በግንባታ ስራዎች ላይ መሰል ተደጋጋሚ አደጋዎች እየተከሰቱ በመሆኑ አሰሪዎችና ሰራተኞች አስፈላጊውን የደህንነት መስፈርት ጠብቀው እንዲሰሩ አሳስበዋል።

ዳጉ_ጆርናል

@Leyu_News
@Leyu_News