Get Mystery Box with random crypto!

አለ_ህግ🔵Ale_Hig

የቴሌግራም ቻናል አርማ lawsocieties — አለ_ህግ🔵Ale_Hig
የቴሌግራም ቻናል አርማ lawsocieties — አለ_ህግ🔵Ale_Hig
የሰርጥ አድራሻ: @lawsocieties
ምድቦች: ብድር, ግብሮች እና ህጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.97K
የሰርጥ መግለጫ

#አለ_ህግ🔵Ale_Hig ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች፣ https://www.youtube.com/@Lawsocieties ሁሉንም ሕጎችና ባለሙያዎች እዚሁ ያገኛሉ🔴 All in one, for All. መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው @LawsocietiesBot / lawsocieties@gmail.com

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-13 15:15:23 DRAFT Value Added Tax Proclamation 2022
https://chilot.me/wp-content/uploads/2022/07/DRAFT-Value-Added-Tax-Proclamation-2022.pdf
Abrham Yohannes

#Share #ሼር
#አለ_ህግ
#Alehig
@lawsocieties
@AleHig
2.0K viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, edited  12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:08:32 አዲሱ የስደተኞች ሕግ

ሕጉ በተለይ ጉዳያቸው በእንጥልል ለነበረ ኢትዮጵያውያንና አፍሪቃውያን እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አንድ የሕግ ባለሙያ ለDW ተናግረዋል።
የጀርመን ጥምር መንግስት በአገሪቱ ላለፉት 5 ዓመታት የቆዩት ስደተኞች ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ የሚያገኙበትን ሕግ አጸደቀ።
ሕጉ በተለይ ጉዳያቸው በእንጥልል ለነበረ ኢትዮጵያውያንና አፍሪቃውያን እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አንድ የሕግ ባለሙያ ለDW ተናግረዋል።
Via DW Amharic
https://p.dw.com/p/4DsNU?maca=amh-Facebook-dw


#Share #ሼር
#አለ_ህግ
#Alehig
@lawsocieties
@AleHig
1.9K viewsEntrust ETC, edited  11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:44:08
Vacancy at MERSA Media Institute(For Fresh Graduate)

Position: Project Associates

Experience: 0 year

Required number of candidate: 8

Qualification: Bachelor’s degree on Information technology, Economics, Law, Medicine, Social Studies or related field of study

Application Deadline: July 23, 2022

ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
Read Detail:- https://bit.ly/3axwXSH
1.9K viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, edited  09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 09:23:59 አቅም በላይ የሆነ ሁኔታ(force majeure)

1 • ከአቅም በላይ የሆነ ሊመልሱት የማይቻል ኃይል

2 • ባለእዳው በምንም መልኩ በቅድሚያ ሊያስበው ወይም ሊገምተው የማይችል ክስተት

ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ ደርሷል የሚባለው ባለዕዳው ባላሰበው ነገር ድንገት ደራሽ ሆኖበት ግዴታውን እንዳይፈጽም ፍፁም መሰናክል በሆነ አይነት የሚያግደው ነገር ባጋጠመ ጊዜ ነው፡፡ በአእምሮ ግምት ባለዕዳው ቀደም ብሎ ሊያስብበት የሚችል መሆኑ የታወቀ አንድ ድንገተኛ ደራሽ ነገር ወይም ለውሉ አፈፃፀም ከባድ የሆነ ወጭ በባለዕዳው የሚደርስበት ቢሆን ከአቅም በላይ የሆነ ኃይል ነው ተብሎ አይገመትም፡፡ ስለሆነም ባለዕዳው ሁኔታው ሊፈጠር ወይም ሊከሰት እንደሚችል ቀድሞ ሊገመት ወይም ሊያስብና ጥንቃቄ ሊያደረግበት የሚችል ከሆነ ሁኔታው ድንገተኛ ደራሽ ነገር ቢሆን እንኳን ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ እንደተከሰተ አይቆጠርም፡፡

ሰ/መ/ቁ.14605 ቅጽ 1፣ ሰ/መ/ቁ. 26565 ቅጽ 5፣ ሰ/መ/ቁ. 85468 ቅጽ 15፣ ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1791፣ 1792፣ 1793 (ሀ) እና (ለ)

የመኪና አሽከርካሪ በሚያሽከረክርበት ጊዜ በመንገዱ ላይ ድንገት ሰው ሊገባ ወይም ድንገተኛ አደጋ ሊያጋጥም ይችላል ብሎ ፈጽሞ አያስብም ተብሎ አይገመትም፡፡ በመሆኑም ድንገት ሰው ሮጦ ወደ በመንገዱ መግባቱ ብቻ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ መኖሩን አያሳይም፡፡

/መ/ቁ. 14605 ቅጽ 1

የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ከአቅም በላይ የሆነ ኃይል ተብሎ ሊወሰድ የሚችል አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 85468 ቅጽ 15

በጉዞ ላይ ያለ ተሽከርካሪ የኤሌትሪክና የመካኒክ ሲስተሙ ድክመት ስለገጠመው በኤሌትሪክ መስመሩ ላይ ከፍተኛ ኃይል ያለው ኬብል ስራውን ስላቋረጠ ከብረት ጋር በመጋጨቱ ምክንያት በተነሳው እሳት ምክንያት ንብረት በቃጠሎ ቢወድም አደጋው አጓዡ ሊገምተውና ሊያስቀረው በማይችል ከአቅም በላይ በሆነ ሀይል ምክንያት የተፈጠረ ነው ሊባል አይችልም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 26565 ቅጽ 5
Ts Md

#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig

@lawsocieties @AleHig

https://t.me/lawsocieties

https://t.me/AleHig
2.0K viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, 06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 20:06:04 #ትግልና እራስን #ነፃ ማውጣት
መጀመሪያ ራስህን ከእሳት ስታወጣ ከአንተ በኋላ ያለውን ትዉልድ ነፃ ታወጣለህ።

አብሬ ልሙት ካልክ ግን አለምን ታጠፋታለህ።

የአመለካከት፣የህይወት ክህሎትና የስኬት መንገድ መጀመሪያ ራስን ለማዳን ከተለመደው አሰራርና አስተሳሰብ ራስን ማዉጣት ነው።
እኛ ሰዎች የተፈጠርነው በአላማና በምክንያት እንጂ ባጋጣሚ አይደለምና።

ስለዚህ ራስህን ከመጥፎ ልማድ ፣ #ከመጥፎ #አመለካከት ፣ #ከመጥፎ አስተሳሰብ ፣ #ከመጥፎ የህይወት ዘይቤ ፣ ከከሳሽነት ፣ #ከአማራሪነት፣ ከተስፋ #መቁረጥ፣ #ከሰበብ ፣ #ከምክንታት፣ #ከስንፍና፣ ነፃ ውጣ......... . ሌሎችንም አዉጣ።
ዛሬውኑ እራስህን አሸንፍ
ያኔ ታሪክህ ይቀየራል ለብዙዎችም ትተርፋለህ።


ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም።
የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 2035(2)

#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig

@lawsocieties @AleHig

https://t.me/lawsocieties

https://t.me/AleHig
2.1K viewsEntrust ETC, edited  17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 19:49:54 ዋስትና

የተጠርጣሪን የኋላ ታሪክ እስክናውቅ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ይፈቀድልን
ተከሳሹ ደጋጋሚ ወንጀለኛ ስለሆነ ዋስትና ሊፈቀድ አይገባም በሚል የምትከራከሩ ዐ/ህግ እና መርማሪ ፖሊሶች እንዲሁም ይህን በምክንየትነት የምትቀበሉ ዳኞች ተከታዩን ግንዛቤ እንድትወስዱ "የተጠቃለሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የህግ ትርጉሞች ከቅፅ1-23" መፅሃፍ መሀል ይህን የሰበር መዝገብ እንደ ማሳያ እነሆ።


የሰ/መ/ቁ.132055፡-በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 67 (ለ) ስር የተደነገገው የዋስትና መብት ገደብ በተከሳሹ ያለፈ የወንጀል ታሪክ ላይ የሚመሠረት አይደለም፡፡

ይልቁንም የድንጋጌው ዓላማ በእጅ ላይ ያለውን የክሱ ሂደት ሊያደናቅፍ ይችላል ተብሎ በሚገመትበት ጊዜ በዋስ የመለቀቅ መብቱን ለመገደብ ነው፡፡ የወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 67 (ለ) ከንዑስ ቁጥር (ሀ) እና (ሐ) ጋር በአንድነት ሊነበብ ይገባል፡፡

ህጉ የተከሳሹን በዋስ የመለቀቅ መብት እየገደበ ያለው በዋስትና ወረቀት ላይ የሰፈሩትን ግዴታዎች አይፈጽምም ተብሎ ሲገመት ወይም ምስክሮችን ሊያባብል ወይም ሊያስፈራራ ይችላል ወይም ማስረጃዎችን ሊያጠፋ ይችላል ተብሎ ሲገመት ነው፡፡

የቁጥር 67 (ለ) ድንጋጌም ከንዑስ ቁጥሮች (ሀ) እና (ለ) ጋር በጣምራ ሲነበብ “ሌላ ወንጀል ሊሠራ ይችላል ተብሎ ሲገመት” የሚለው ድንጋጌ ከተያዘው ክስና ከተጀመረው የፍርድ ሂደት ጋር በተያያዘ ጠባብ የህግ ትርጉም በተጣጣመ መልኩ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡

ፍ/ቤቶቹ የተከሳሽችን ያለፈ የቅጣት ውሳኔ አሁን ከተከሰሰበት ጉዳይ ጋር በማያያዝ በዋስ ቢለቀቅ ተመሳሳይ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል የሚል ግምት በመውሰድ የዋስትና ጥያቄውን አለመቀበል አግባብ አይደለም፡፡

በተጨማሪም በሌላ በኩል የወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 138 (1) ህጉ በግልጽ ካልተደነገገ በቀር ተከሳሹ በፍርድ ዳኝነት በግልጽ እስካልታወቀ ድረስ የቀድሞ ጥፋተኝነቱ አይገለጽም ሲል ደንግጓል፡፡
ድንጋጌው የተከሳሽን ንጹህ ሆኖ የመገመት ህገ-መንግሥታዊ መብት የሚያመለክት ሲሆን በተጨማሪም ዳኞች የወንጀል ጉዳይ በሚመረምሩበት ጊዜ በተከሳሹ የጥፋተኝነት ሪከሪድ ጫና አድሮባቸው የተሳሳተ ውሳኔ እንዳይሰጡ ለማድረግ የሰፈረ ነው፡፡

በመሆኑም የተጠርጣሪዉ የቀድሞ የጥፋተኝነት መዝገብ በጊዜ ቀጠሮ ጊዜ ሲቀርብ ፍ/ቤቶች ከላይ በተጠቀሰው የህግ ድንጋጌ መሠረት እንዳልቀረበ በመቁጠር ሊወሰን ይገባል እንጂ ህጉን በመጣስ በተጠርጣሪዉ የቀድሞ የጥፋተኝነት መዝገብ ላይ በመመሥረት ማከራከር እና መወሰን መሠረታዊ የህግ ስህተት ነዉ፡፡

በአጠቃላይ የአንድ ተከሳሽ ያለፈ የቅጣት ውሳኔን አሁን ከተከሰሰበት ጉዳይ ጋር በማያያዝ በዋስ ቢለቀቅ ተመሳሳይ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል የሚል ግምት በመውሰድ የዋስትና ጥያቄን አለመቀበል አግባብነት የለዉም፡፡እንዲሁም በህግ በግልጽ ካልተደነገገ በቀር አንድ ተከሳሽ በፍርድ ዳኝነት በግልጽ እስካልታወቀ ድረስ የቀድሞ ጥፋተኝነቱ ሊገለጽ አይገባም፡፡ቅጽ/23

via #henoktaye law office

#አለ_ህግ #Alehig

@lawsocieties @AleHig

https://t.me/lawsocieties

https://t.me/AleHig
2.2K viewsEntrust ETC, edited  16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 20:23:15 Draft Criminal Procedure and Evidence Code @Lawsocieties
https://chilot.me/2022/07/11/draft-criminal-procedure-and-evidence-code/
2.6K viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, edited  17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 20:22:52 Private Organization Employees’ Pension Proclamation No. 1268-2022
@Lawsocieties
https://chilot.me/2022/07/11/private-organization-employees-pension-proclamation-no-1268-2022/
2.5K viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, edited  17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ