2022-07-14 19:59:58
ማስታወቂያየኢፌዴሪ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያየ መንገድ ገብተው የሚንቀሳቀሱ የውጭ አገር ዜጎችን የመመዝገብና የመቆጣጠር ስልጣን በአዋጅ ቁጥር 354/1995 እና ደንብ ቁጥር 114/1997 የተሰጠው ተቋም ነው።ስለሆነም፣
• በተለያዩ የቪዛ ዓይነት ወደ ኢትዮጵያ የገባችሁና ቪዛችሁ የሚፀናበት ጊዜ ያለፈበት፤
• የመኖሪያ ፈቃዳችሁ የሚፀናበት ጊዜ ያለፈበት፤
• ምንም አይነት ቪዛም ሆነ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላችሁ፣
• በኢ.ፌ.ዴ. ሪ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኝነት ወይም የጥገኝነት ጠያቂ ዕውቅና አግኝታችሁ በከተማ ስደተኝነት በፈቃድም ይሁን ያለፈቃድ በአዲስ አበባ እና በዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የምትኖሩ የውጭ አገር ዜጎች በሙሉ፡-
አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ከሐምሌ 11 እስከ 25/2014 ዓ.ም ድረስ ምዝገባ የሚያካሂድ ስለሆነ፤ ዘውትር በስራ ሰዓት ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ በሁሉም ስራ ቀናት ማንነታችሁን የሚገልፅ ሕጋዊ ሠነድ /ፓስፖርት፣ የመኖሪያ ፈቃድ፣ የስደተኛ መታወቂያ ወይም የምዝገባ ማረጋገጫ ሰነድ ፣ የጉዞ እና/ወይም ሌሎች ተያያዥ ሠነዶችን/ ይዛችሁ በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጥሪ ያቀርባል፡፡
የምዝገባ ቦታ፦
• በአዲስ አበባ ከተማ፡- በሁሉም የወረዳ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ጽ/ቤቶች እና ፒያሳ በሚገኘው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት፣
• በፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች፡- ገላን፣ ዱከም፣ ለገጣፎ፣ ሱሉልታ፣ ቡራዩ፣ ሆለታ እና ሰበታ
እንዲሁም ቢሾፍቱ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ፅ/ቤቶች ናቸው፣
ከላይ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ባልተመዘገቡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
ማሳሰቢያ፡- የውጭ ዜጐችን በመቅጠር የምታሰሩ፣ በቤታችሁ ተከራይቶ ወይም በጥገኝነት የምታኖሩ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ መመዝገባቸውን እና የምዝገባ ማረጋገጫ መውስዳቸውን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን።
ለበለጠ መረጃ ድረገፃችንን ይጎብኙ፡- www.invea.gov.et.
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
Notice
The Immigration and Citizenship Service of the Federal Democratic Republic of Ethiopia is mandated to register and administer legal permits for foreign nationals living in Ethiopia according to Proclamation No. 354/2003 and Regulation No. 114/2004. As a result, to make legal processes the Immigration and Citizenship Service announces this registration.
Therefore, all foreigners with:
• Expired visas;
• Expired Residence permits; and
• Those without any visa or residence permit;
• As well as refugees or asylum seekers requesting status and residing in Addis Ababa and its vicinities with or without an urban refugee permit;
Should register in person between July 18 to August 01, 2022 in all days at work hours including Saturday and Sunday by bringing legal documents that testify your personality (Such as - passport, resident ID, Refugee ID, Proof of Registration, and/or any travel documents).
Place of Registration: -
• Addis Ababa: Vital Events Registration Offices of all Woredas and Immigration and Citizenship Service, Piazza Office;
• Oromia Special Zone within the vicinity of Addis Ababa: Vital Events Registration Offices at Gelan, Dukem, Lege Tafo, Sululta, Burayu, Holeta, Sebeta, and Bishoftu town.
The Immigration and Citizenship Service would like to notify you that it will take legal measures against those who fail to register on the dates mentioned in this notice.
Remark: - Those who hire and give shelter or rent a house to foreign Citizens should follow up their registry and make sure whether they take proof of registration.
For further inquiries, please visit our website: - www.invea.gov.et.
Immigration and Citizenship Service
Addis Ababa, Ethiopia.
#Share #ሼር
#አለ_ህግ
#Alehig
@lawsocieties
@AleHig
https://t.me/lawsocieties
151 viewsLawyer Mike የህግ ባለሙያ, edited 16:59