Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ kinexebebe — መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ kinexebebe — መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @kinexebebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.36K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡
ግጥሞች
መነባነቦች
ከዚያም ከዚህ
እናስተዋውቃችሁ
፡ ጭውውት
ድራማ.... ወዘተ
ለሀሳብ @ty1921 ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-17 09:06:30 ++ ሥነጽሑፍ - ግጥም !

( ርዕስ - ምን አሉ ? )

ምን ነበር ያሉት አበው ሲናገሩ
የታሪክ አደራ የቅርሳቸው ክብሩ
ለምን ነበር ይጨነቁ የነበሩ
ስለምን ነበር ያስቡ የነበሩ
ስጋቸውን ለማስደሰት
ያመረና የጣመ ለመብላት
በእስፕሪንግ አልጋ ላይ ለመተኛት
ቢሮ ተቀምጦ ዳቦ ለመብላት
ባለስልጣን ሆነው ለመታየት
ስለምን ነበር ሲያስቡ የነበሩት
ስለምን ነበር ሲናገሩ የነበሩት
ምን ተብሎ ተጽፎ ስለ እነርሡ ክብር
ምን ተብሎ ታወሰ የእነርሡ ዝክር
ብርሀናው ይውጣ ይነገር ሥራቸው
ዳግም ይነገር ይታይ ውጤታቸው
ብርሀናው ከወጣ ከተፈለገ ሥራቸው
አስታዋሽ ካገኛ ከታየ ሥራቸው
እንዲህ ነበር አበው የታሪክ ገድላቸው
ገና ጉዞውን ሲጀምር የክርስትናውን
ከሰባት ወንድሞች ጋር በአበው የተሾመው
ያ ታለቅ አባት የወንጌል አርበኛው
በአንድ ስብከት 12ሺህ ያተመቀው
ምን አለ እስጢፋኖስ በድንጋይ ሲወግሩት
ስጋውን ቆራርጠው ደሙን ሲያፈሱት
እንደ ስንዴ ክምር ድንገይ ሲጭኑበት
ስለምን ተናገረ ምና ብሎ መሰከረ
ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍስን ተቀበል
ጌታ ሆይ ይህን ኃጢያት አትቁጠርባቸው
ያ አረጋዊ ታላቅ አባት
ጌታን የሚወደው ከሁሉ በፊት
ሲናገር ቀደም ቀደም ብሎ የሚመሠክረው
ከጌታ ስብከት ለአፍታ ያልተለየው
አንተ ከምትሞት እኔ ልሙት ያለው
የመንግስተ ሰማያት ቁልፍ አደራ የተሰጠው
በጎቹን እንዲያሰማራ ቃል የገባው
ለመሆኑ ምን አለ ጴጥሮስ ያ ታላቁ አባት
ጌታ ሆይ ወዴት ትሄዳለህ ደግመኛ
በሮም አደባበባይ ልሰቀል ሲለው
ጌታ ሆይ አንተ ከምትሰቀል እኔ እሰቀላለሁ
ስለመንግስተ ሠማያት ሲከራከሩ ሀዋሪያት
ጌታችን በምሳሌ የነበረው አቅርቦት
ያ ታናሽ ብላቴና ያልተለየው ከዮሐንስ
የሠማውን ለማስተላለፍ የተሯሯጠው በእግር በፈረስ
ምን አለ አግናጢዎስ ለባሴ እግዚአብሔር ምጥው ለአንበሳ
በትርኢት ቀርቦ በሮም አደባባይ ሲሰዋ
ዛሬ ተረኛ ነኝ በአምላክ እንደንጹህ መገበሪያ ስንዴ ልቀርብ ይገባኛል አለ
በ451 በጉባኤ ኬልቄዶን
እንዲቀበል ተገደደ ሁለት ባህሪይን
በበክርሊያና መለቂያ በሀይል የታዘዘው
ወልድ ዋህድ አንድ ባህርይ ብሎ የመሰከረው
የበርክሊያንና የመርቂልያን ዱላ የጠገበው
በግዞት የተሰደደው
ጥርሱ በግፍ የወለቀው
ፅህሙ በግፍ የተነጨው
ምን አለ ዲዮስቆሮስ ያ ታላቅ ባለሙያ
ምን ብሎ መሰከረ ስለምንስ ተናገረ
ጥርሱንና ጽህሙን በመሀረብ አስሮ ክርስቲያኖች
ይህ የሀይማኖት ፍሬ ነው በርቱ አይዟችሁ
ምን አለች ያቺ ታላቅ እናት
በስጋ ስትኖር ዓለምን የናቀች
ምን ያደርግልኛል ብላ በልጅነቷ የመነነች
የሰውን ልጅ ከአምላክ ለማስታረቅ የበቃች
ደግሞም ሰይጣንን ለማስታረቅ የለመነች
የዓለምን አምልኮት ታግላ ያሸነፈች
ለስጋዋ ሳይሆን ለነፍሷ የቆመች
ለብልጭልጭና ለጌጥ እጇን ያልሰጠች
በአጓጉል ፋሽን ያልተንበረከከች
በስጋዊ ምኞት በሀይሏ የገደለች
ለመሆኑ ምን አለች ክርስቶስ ሰምራ
ዘብሄረ ቡልጋ የኢትዮጲያ የቅርስ አደራ
ሳጥናኤል ሆይ ሳጥናኤል ሆይ ና ውጣ
ከአምላክህ ጋር ላስታርቅህ ማነው
በክብር ስሜ የጠራኝ ብሎ ሲናገር ሚካኤል ደርሶ በሰይፍ መታው
ይህ ነበረ የአበው ገድላቸው
የቅድስና ስራ የክብር ጌጣቸው
ይሄን ነበር ያሉት አበው በቃላቸው
ለትውልድ እንዲተላለፍ የፃፉት በደማቸው
ስጋቸውን ቆርሰው አጥንታቸውን የሰበሰቡት
ህይወታቸውን ለክርስቶስ እንደስንዴ መገበሪያ የሰጡት
ኸረ ዛሬስ ምን አለን እኛ
የአበው ልጆች የተቀበልን አደራ
በእነርሱ እግር ለመተካት የጀመርን ስራ
ምን ነበር ስራችን ጌጥ ክብራችን
ስለምን ነበር ሀሳብ ጭንቀታችን
የእኛ ጭንቀትማ እንደው ከተነሳ
ስጋን ለማስደሰት የምናየው አበሳ
ድንቅና ውብ አድርጎ በፈጠረው አካላችን
ይበልጥ ለማሳመር ስናደርግ አዲስ ፋሽን
ግድግዳ ይመስል ቀለም ስንቀባው
የጠቆረውን ለማቅላት ብራውን እያልን ስንከልሰው
በዓለም ፋሽን ይበልጥ ስናጌጠው
እንደልኳንዳ ቤት ስጋ በመቶ ሻማ ስናሳየው
ይሄ ነው ጭንቀታችን ሀሳብ ክብራችን
ለመሆኑ ምን አላችሁ መናፍቅ ቤታችሁ ሲገባ
ወንጌል ተሰበኩ ብሎ ሊላችሁ አላስወጣ አላስገባ
ምን ብላችሁ መለሳችሁ ስለምንስ አወራችሁ
ጀርመናዊ በንዴ ወንጌልን ለመስበክ ሲመጣ
ከተማራችሁት ውጭ አዲስ ቃል ሲያመጣ
ምን ብላችሁ መለሳችሁት ይህን መናፍቅ
ዘመቻ ተብሎ በአንድ ቃል ሲታወጅባችሁ
መዳን አለባችሁ ተብሎ ሲሰብክላችሁ
ቃሉን አልሰማችሁም ስሙ ስትባሉ
ለመሆኑ ምን አላችሁ
ከአበው አባቶች የተቀበልነውን አደራ
እንድንወጣ አምላክ ይሁን ከእኛ ጋራ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን !
@kinexebebe
2.0K views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 09:05:46 ሳልፆም ሊፈሰክ ነው
መንፈሳዊ ግጥም

አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር
@kinexebebe
1.8K views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 10:27:33 ጸሎት

፩. ጸሎት ከክፉ ነገር ይጠብቅሃል፤

፪. ጸሎት በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ እንድትኾን ያደርግኻል፤

፫. ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ይበልጥ ያቀርብኻል፤

፬. ጸሎት ደስተኛ ያደርግኻል፤

፭. ጸሎት ተስፋን ይሰጥኻል፤

፮. ጸሎት የራስ ወዳድነት ስሜትኽን ይቀንስልኻል፤

፯. ጸሎት ከኹሉም ስቃዮች ይፈውስኻል፤

፰. ጸሎት ፈተናን ለማሸነፍ ይረዳኻል፤

፱. ጸሎት በመንፈሳዊ ሕይወትኽ ጠንካራ እንድትኾን ያደርግኻል፤

፲. ጸሎት ነገሮችን ይለውጣል።

@kinexebebe
@kinexebebe
@kinexebebe
2.0K views07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 13:39:36 ✟ ስለ ጾም ብሂል
ጾም የትሩፍት ሥራ መጀመሪያ የጽሙዳን ክብራቸው ናት፡፡
/ ማረ ይሰሕቅ/

በትጋህ ሌሊት ጊዜ መቆም መስገድ ባይቻልህ በአልጋህ ላይ ተቀምጠህ ሳለህ ትጋህን ይዝ ተገኝተህም ቢሆን ሁለት ቀን ወይም ባይቻልህ እስከ ሠርከ ጹም ፡፡
እስከ ሠርክም ወጾም ባይቻልህ መጥነህ ተመገብ እስክትጠግብ እንዳትመገብ ተጠበቅ
/ አቡነ ሺኖዳ/

☞ ይህን ዓለም ማሰብ በመዓልት እንዲዋጋን እንዲሠለጥብን የታወቅ ስለሆነ ዘወትር ጾምን ጽኑ ጋሻ ልንይዝ ይገባል ፡፡
/ ዮሐንስ አፈወርቅ /

☞ የአንደበት ጾም ከአፍ የተሻለ ነው ፡፡ የልብ ከፍትወት መከልከል ደግሞ ከሀሉም የተሻለ ነው ፡፡
/ ቅዱስ ይሰሕቅ /

☞ ጾም መከታ ነው ማንኛውም ሰው የዲያብሎስ ኃያል መመከት አለበት ፡፡
/ ቅዱስ እንድርያስ /

☞ አንድ ንጉሥ የጠላቶቹን ከተማ ለመይዝ ከፈለገ በመጀመሪያ ማድረግ ይለበት የጠላቶቹን የውኃና የምግብ መስመር ሙሉ ለሙሉ ማቋረጥ ነው ፡፡ በሥጋም ቢሆን ልክ እንደዚሁ ነው ፡ አንድ ሰው ሲጾም በጣም ስለሚርበው የነፍሱን ጠላቶች ፈጥነው ይደክማሉ ፡፡
/ ዮሐንስ ሒጺር /
@kinexebebe
@kinexebebe
@kinexebebe
2.2K views10:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 08:44:02 ይድረስልኝ
ፍቅር ይዞኛል ለምትሉ ሁሉ
..........................................................
አንተ ፍቅር ይዞኛል የምትለው፤ አዎ አንተ በፍቅሯ አብጃለው፣ ስነሳም ስተኛም ስለእርሷ ነው የማስበው የምትለው! በዓይኗ ሰረቅ አድርጋ ድንገት ስታየኝ ልቤ ቀጥ ይልብኛል የምትለው፤ እስቲ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ? አያድርገውና በመጀመሪያ ያየሃት ቀን ያፈዘዘህ ዓይኗ ቢፈስ፣ ቀልብህን ስቦ ያስደነገጠክ መልኳ ቢጠቁር እና ቢጠፋ፣ እስከ ወገቧ የረዘመው ፀጉሯ ቢቆረጥ፣ አቅርበሃት ጓደኛህ ካደረካት በኋላ የወደድክላት ፀባዩዋ እና ሥርዓቷ ተለውጦ ክፉ እና ደረቅ ብትሆንብህ፣ አንጀትህን ያርሰው የነበረው አረማመዷና ቅልጥፍናዋ በበሽታ ተቀምቶ አልጋ ላይ ሆና ብታቃስት አሁንም ከእርሷ ጋር ትሆናለህ? እንደ ድሮ ከእርሷ ጋር ለመሆን ትሽቀዳደማለህ? ሁሌ እንደምታፈቅራትና እንደምትሳሳላት መንገርህን ትቀጥላለህ? ለእርሷ የምታሳየው ትህትናና ክብር ይቀንስብሃል? አንቺስ ብትሆኚ? መጀመሪያ ያየሽው ዕለት ደስ ያለሽ መልኩና ቁመናው እንዳልነበረ ቢሆን፣ ሁሌ አንቺን ለማስደሰት ብሎ አንቺን በመጋበዝ እና በማዝናናት ያጠፋው የነበረው ገንዘብና ሀብት ጠፍቶ ፍጹም ደሃ ቢሆን፣ መጀመሪያ የተዋወቃችሁ ሰሞን ሲያሳይሽ የነበረው ፍጹም ትህትና እና አክብሮት ተለውጦ በትዕቢት አንቺን መማታት ቢጀምር፣ ጤንነቱን አጥቶ በበሽታ ቢንከራተት፣ በመጀመሪያ ወደ እርሱ ስቦ ያመጣሽ ነገሮቹ ሁሉ ቢጠፉ አሁንም ከእርሱ ጋር ትሆኚያለሽ? አሁንም እርሱ ጋር ስልክ መደወልሽን ትቀጥያለሽ? እህቴ ሆይ እስቲ ንገሪኝ፤ ፍቅርሽ ከአፍሽ ነው ወይስ ከልብሽ? ወንድሜ ሆይ ልጠይቅህ፤ ፍቅርህ በመናገር ነው ወይስ በተግባር?

መልሳችሁ " ይህ ቢፈጠር አብሬ አልቀጥልም" ከሆነ ከመጀመሪያውም ፍቅር እንዳልያዛችሁ ላርዳችሁ እወዳለሁ፡፡ ስትተያዩ እወድሃለሁ፣ እወድሻለሁ ከምትባባሉ ባየሁሽ/ ባየሁህ ቁጥር በውስጤ ያሉት ንጥረ ነገሮች (hormones) ይንተከተካሉ ብትባባሉ የተሻለ ነው፡፡ ምክንያቱም የፍቅር ትርጉም ይህ አይደለምና፡፡

ፍቅርማ ምን እንደሆነ ራሱ ፍቅር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በሚገባ አስተምሮናል፡፡ እርሱ ከምድር አፈር ካበጃጀን በኋላ የሕይወትንም እስትንፋስ እፍ ካለብን በኋላ ፍጥረት ሁሉ መልካም እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ ያኔ አምሮብን፣ ተከብረን ሳለ ወዶናል፡፡ እፀ በለስን በልተን ያበራ የነበረው የጸጋ ልብሳችን ተገፎ ራቁታችንን ስንሆን፣ ደዌ የማያውቀው ሥጋችን በከንቱ ፍትወታት ሲታመምም በፍጹም ፍቅሩ አፍቅሮናል፡፡ ይተወንም ዘንድ ስላልቻለ ፍቅርን ፍቅር ከዙፋኑ ስቦ ስለእኛ እስከ ሞት አደረሰው፡፡ ታመን በኃጢአት አልጋ ተኝተን ሳለ ከጎናችን ሳይለይ ያሳታመመን አምላካችን ነው፡፡ እስከመጨረሻው ድረስ በኃጢአት የከረፋነውን ሳይጸየፈን ተጠግቶን ቁስላችንን በቁስሉ ያከመን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ሊያክመን መጥቶ እንኳን እኛ አልተቀበልነውም፡፡ ቁስላችንን ሳይጸየፍ የቀረበንን ፈጣሪያችንን መታነው፡፡ ኑ ላድናችሁ ሲለን በመስቀል ላይ ሰቀልነው፡፡ ሐኪሙን የሚሳደብና የሚማታ በሽተኛ እንደምን ያለ ነው? የበሽተኛውን ስድብ እና ድብደባ ታግሶስ በትጋት የሚያክም ሐኪም እንደምን ያለ ነው? ለዚህስ አንክሮ ይገባል!!

ወዳጄ ሆይ ፍቅር በደስታ ጊዜ ኖሮ በኃዘን ጊዜ የሚጸና፣ በጤናው ጊዜ አብቦ በደዌ ጊዜ የሚፈካ፣ በሰላም ጊዜ ተኮትኩቶ በጭንቅ ጊዜ የሚበቅል ረቂቅ የአምላክ ስጦታ ነው፡፡ ታድያ ወዳጄ ሆይ በፍቅርሽ ተይዣለሁ ያልካት ሚስትህን ያማረው መልኳ በድንገት ቢጠፋስ ብለህ የምትጨነቅ ከሆነ እንዴት እወዳታለሁ ልትል ትችላለህ? ጤናዋን አጥታ አልጋ ላይ ብትተኛ ጥለሃት ለመሄድ የምታስብ ከሆነ እንዴት እወድሻለሁ ልትላት ትችላለህ? አንቺስ ብትሆኚ፤ ፀባዩ እንዳለ ተለውጦ ቢንቅሽና ቢያቃልልሽ ትተሽው ለመሄድ የምታስቢ ከሆነ እንዴት ዓይኑን እያየሽ እወድሃለሁ ትይዋለሽ? ቢመታሽም እንኳን እንደ አምላክ ምቱን ታግሰሽ እርሱን ለማከም ካልፈቀድሽ እንዴት አፈቅርሃለሁ ትይዋለሽ?

" ፍቅር ያስታግሳልና"(1ኛ ቆሮ 13÷4) የማትታገሱ ከሆነ እንዴት ፍቅር ይዞኛል ትላላችሁ? አምላክ ያሳየንን ፍቅር ለሌሎች በመስጠት ክርስቶስን ልንመስለው ይገባናል፡፡ እህቴ ሆይ ወዳጅሽ በክፉ ሱስ ተጠምዶ፣ በትዕቢትና በንቀት ልቡ ተነድፎ ገብቶ ቢያንቋሽሽሽ ለእርሱ የምትሰጪው ፍቅር እንዲጎድል አትፍቀጂ፡፡ የፈለገ ተለውጦ የማታውቂው ሰው ቢሆንብሽም ለእርሱ የምትሰጪውን እንክብካቤ በትጋት ፈጽሚ፡፡ ያለንግግር ፍቅርሽን የሚነግሩትን ዓይኖችሽን ከዓይኖቹ አታንሺ፡፡ ወንድሜ ሆይ የሚስትህን የምትወድላት ፀባዩዋን ረስታ ደረቅና የምታውክ ብትሆንብህ እንኳን በስስት የምታያትን የፍቅር መመልከት አትንፈጋት፡፡ አምላክስ በሕመማችን ጊዜ ዓይኑን ከእኛ ድንገት ቢያነሳ ኑሮ ወድቀን እንደምንቀር ሁሉ አንተም ዓይንህን ከሚስትህ ላይ አታንሳ፡፡ ጌታ በፍጹም ፍቅር ወዶናልና እርስ በርሳችሁ በሚያስታግሰው እውነተኛው ፍቅር ተዋደዱ፡፡ በፍቅርም ቃል ተነጋገሩ እንጂ አትቆጡ፡፡

ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ የአፍ ብቻ ሳይሆን የልቡና፣ በመናገር ብቻ ሳይሆን በተግባር የምንገልጠው እውነተኛውን ፍቅር ስጠን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
@kinexebebe
@kinexebebe
@kinexebebe
2.4K views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 13:40:42
እንኳን ደስ አለክ መምህራችን ያስተማርከንን በተግባር አሳየከን
1.7K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 09:07:50 ++ ኪነጥበብ - በልሃ ልበልሃ !!


ሁለት ሰዎች ከተለያየ ቦታ ሲመጡ መድረክ ላይ ይታያሉ የሁለቱም ሰዎች ማለፊያ መንገድ አንድ በመሆኑ መንገዱ አጠገብ ያለው ድልድይ ደግሞ የሚያሳልፈው አንድ ሰው ብቻ ነው፡፡ በዚያ አገር ባህል እና ወግ ደግሞ ሁለትሰዎች እዚያ ድልድይ ላይ ከተገናኙ በልሃ ልበልሃ ተባብለው ያሸነፈው ሰው በቅሚያ ያልፋል፡፡ ይሕም ነገር አሁን ተከሰተ፡፡


እንግዲህ ወንድሜ ባገሩ ወግና ባህል
በልሃ ልበልሃ እንባባል ቀዳሚው እንዲለይ

ምን ገዶኝ ወንድም ጃል
የቀየው ባህልና ወግ አይደል
ታዲያ ቀዳሚው እንዲለይ
በዕጣ መጣጣል ብንለያይ
እኔ ግን በእድሜም ከፍ ስለምትለኝ
አንተ ብትቀድም ነው የሚበጀኝ

ስላከበርከኝ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው
እንግዲህ በልሃ ልበልሃ ልጀምረው
በልሃ ልበልሃ
ካልመለስክ ልቅጣሃ

በላሃ በለኛ
ካልመለስኩ ቅጣኛ

ከሲና በርሃ ተነስቶ
ሃመልማል ሳይቃጠል አይቶ
ምንም አፉ ጎልዳፋ ቢሆን
እግዚአብሔር ለክብሩ መገለጫ ያሳየን
በዘጠኝ ተአምራት በአስረኛ ሞተ በኩር
የአምላክን ሕዝብ ከፈርዖን አገዛዝ ያስጣለ በተአምር
የስራኤልን ሕዝብ የመራ
ማነው ስሙን ጥራ?

እሱንማ መች አጥቼው
እናቱ ሸሽጋ በሳጥን ያኖረችው
የፈርዖን ልጅ አግኝታ በፍቅር ያቀፈችው
ያ መልከ መልካም እንቦቀቅላ
ፍትፍቱን ትቶ እሳቱን የበላ
የአምስት መፅሐፍ ፀሐፊ የተባለው
ሊቁ ታላቁ አባት ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነው፡፡

ትክክል ብልሃል መልሱንም አውቀሃል
በል ተራው ያንተ ነው ጥያቄህ የታል



በልሃ ልበልሃ
ካላወክ ልቅጣሃ

በልሃ በለኛ
ካላወኩ ቅጣኛ

አርጢሞስ አምላክ ሳትሆን ተቀራፂ ምስል
ባንዴ የምትፈርስ በእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል
ብሎ ባመሰስተማር ለእስር የበቃሁ
በፈላም ውሃ ውስጥ የተቀቀለም ነው
ይሔም አልበቃውም ንጉሱም ጨካኝ ነው
በፍጥሞ ደሴት ውስጥ በግዞት ያለ ነው
በዛ ውስጥ እያለ አንድ ነገር ሰርቷል
የሰራሁስ ስራ? ስሙስ ማን ይባላል?

ይህንን ካላወኩ ምኑን አወኩ ሊባል
ባጭሩ ልንገርህ ኤሊያስም አይደል

ፍፁም ስህተት ነው መልሱም ይህ አይደል
ቅጣትህን ተቀበል

ይሔው ለቅጣቴ ጎንበስ ቀና ብዬ
ባለማወቄማ ልቀጣ ጌታዬ

አቡነ ዘበሰማያት ይደገም ግዕዙ
እሱን ካላወቁ ሌላ ይታዘዙ

ይሔው ልጀምረው ያደኩበትን
ከየኔታ እግር ስር የተማርኩትን
አቡነ ሰበሰማያት …….

በትክክል ነው ግዕዙንም ያልከው
የጥያቄዬን መልስ ስማኝ ልናገር ነው
በፍጥሞ ደሴት ውስጥ በግዞት ተቀምጦ
ራዕዩንም ፃፈው ብራናውን ገልጦ
የዚህ ታላቅ አባት ስሙም ክብር ያለው
ቅዱስ ዮሐንስ ነው ደቀ መዝሙሩም ነው
እንግዲህ አሁንም ጠያቂው እኜ ነኝ
በልሃ ልበልሃ
ካላወክ ልቅጣሃ

በልሃ በለኛ
ካላወኩ ቅጣኛ

በጎጃም ሃገር በዳማ ሥላሴ
አንድ ፀሐይ ወጥታ ታዛዥ ለሥላሴ
በ7 አመቱ ብርሃኑን አጥቶ
ለአምስት አመት ቆየ በጸሎት በርትቶ
ጌታ አምላካችን በአካል ተገልፃል
አዳኝ በመሆንህ ዓይንህ ይስራ ተመልሶ
ይሔንንም ሰጠው 12 አክናፍ
ዓለምን ይዞራል በመፍጠን
ታዲያ ይህ አባት ስሙን በል ጥራልኝ
እውቀትህን ገልጸህ ለይተህ አሳየኝ

ማንም አይረሳቸው አባ ዘርዐብሩክ
ሐይን ያቆሙ ታላቅ አባት ናቸው
ለወንዝ መፅሐፍን ባደራ የሰጡ
በጸሎት በስግደት የኖሩ ሳይወጡ
የዞንዶ ጥርስ ሳይቀር አስታርቀው ሲቆጥሩ
እንዴት ይረሳሉ እኝህ ታላቅ አባት
ይደርብን ዘውትር የእሳቸው በረከት

በእውነት ልክ ነው ፍፁም የለው ስህተት
እንዴት ይረሳሉ እኝህ ታላቅ አባት

በል እንግዲህ ያሸነፍኩ እኔ ነኝ
ድልድዩን ልቀቅ በሰላም አሻግረኝ

ይሔው ለቀኩልህ በሰላም ተሸገር
ካሸነፍከኝማ ላንተ ይሁን ክብር
ወጉ ማዕረጉን አልጥስ
አንተ እኮ ነህ ንጉስ

ወጉን ማዕረጉን የሚቀድመው አለ
ማክበር መከባበር የኢትዮጵያውያን ወጋቸው አይደለ
አንተም እኮመ እኔን በእድሜዬ ሰትበልጠኝ
በጥያቄው ሳይሆን በእድሜዬ አሸነፍከኝ


ሁለቱም ሰዎች ተሳስመው ተመራርቀው በእድሜ የሚበልጠው ሰውዬ ቀድሞ ይሻገራል ቀጥሎ ተሸግሮ ወጥቶ ይሔዳል።
@kinexebebe
2.4K views06:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 08:36:42 https://t.me/webzema
1.6K views05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 13:52:42 ++ ኪነጥበብ - መነባንብ !!

( ማነው ቃሉን የተረዳ? )

ጆሮው ሀጥያትን የጠላ.....
የፅድቅ ህይወት ቃል የጠራ
የወንጌልን ድምፅ የለየ
በምኞት ኩነኔ ያልገበየ
ማነው እርሱ ይህ የሚያደርግ ?
የፅድቅ አክሊል ባለ ማዕረግ
ትሁት እና ቅን አድራጊ በምግባሩ ፋና አዋቂ
ቅድስና ያለው ዛሬ ባለ 60 100 አመርቂ።
ለንስሐም ያልዘገየ ....
በሐሜት ማጥ ያልጨቀየ
የሚሰብክ በምግባሩ
ያላደፈ በጅምሩ
እያወቀ የሀጥያት ደሞዝ ያልቀየረ እምነቱ
ተደራድሮ በትሩፋት የሚታደግ ሰውን ከጥፋቱ
ማነ ው ወዳጅ ? ማነው ቅኑ? የሚታመን በዘመኑ።
የጊዜአችን ሰማዕትነት
የራስ እምነት ብርቱ ጠላት
ዝሙት በልቡ ያልነገሰ
መቅደስ ልቡ ያልረከሰ
ነፍሱን ለሞት ያልሸጠው
የአለም ማዕበል ያልዋጠው
እየኖረ በትህትና በአፍላ ዘመን በጉብዝናው።

በወጣትነት አደብ ገዝቶ
ያተረፈው መክሊት በዝቶ
በሉ ጥሩት ይህ አይነቱ
ይናገረኝ የህይወቱ
ትዕዛዛቱን የጠበቀ
ወንጌል አንድምታን የለየ
በፆም በፀሎት የተጋ
ለክደት ልቡ የተዘጋ
እየረታ መናፍቁን
የሚያስታርቅ ሊቅ ደቂቅን
መልስ ሰጪ ወንጌላዊ
ተስፋ ግቡ ሰማያዊ
ሰው ናፈቀኝ ሰው እሻለው
ሰው ካለበት ምድር ካለው።
ይህ አይነቱን ከኣያችሁት
የሚጠራህ አለ በሉት
እሔዳለሁ እስከአለበት
ባዶነቴን እንዲሞላት።

ቅዱሳን አበውን የመሰለ
ስለ አምላኩ ፍቅር የቆሰለ
አንገቱን ለእምነት ሰይፍ የለገሰ
በሞቱ ትንሳኤውን ያስታወሰ
ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ጳውሎስ
ሰማዕቱ እስጢፋኖስ
አባ እንጦንስ አባ አርሳኖስ
የወንጌል ሰው ጎርጎርዮስ
የተዋህዶ መሰረቶች
የድል አክሊል ባለ ሀብቶች
ተጋድሏቸውን የደገመ
የዕምነት ረጫውን የፈፀመ
ያባቱ ልጅ ይህን መሳይ ሰው
የለ እንደሆነ ባሰታውሰው።
ፈጣሪ አምላኩን ያልካደ
የልቡ የዕምነት ግንብ ያልነደ
በጠንቋይ ደጅ ያልቆመ
ስጋው አማልክት ያልሾመ
ያልተሳለመ እግሩ
ያልገበረለት ብሩ
የእድፉን እጣቤ ያልጠጣ
ህይወቱን በመቅሰፍት ያልቀጣ
አው ልክ ነው እርሱ
ማደርያ አላት ነፍሱ።

የአምላክ ቁጣ በዝቶ
ፅድቅ በምድር ከስቶ
ምህረት ከሀገር ሲርቅ
ሰውም አምላኩን ሲርቅ
ሀጥያትን ሽቶ ትውልድ
እምነት ምግባሩን ሲንቅ
አለም ተሞልታ በአመፅ
መዳን ተስኗት ከለምፅ
ማነው ይሔን የለየ
ከቃሉ ያልተለየ
በማያምኑት ላይ ያልቀና
ሰንበትን አክብሮ የፀና
የሀጥያት ውበት የናቀ
ስጋው ከስጋ ሞት የራቀ
እናት አባቱን አክባሪ
የወንጌል ህይወት ነዋሪ
እጁን ለስርቆት ያልሰደደ
ከእውነት ሚዛን ያልወረደ
በወዳጁ ወዝ ያልገመጀ
ለስንፈናው ሰበብ ያላበጀ
ፍቅረ አምላክ ፍቅረ ሰብ የተረዳ
ስለ ወንድሙ ሲል እራሱን የተጎዳ
ህይወቱ በምግባር የተዋበ
አፉን ከሀሰትነት ቃል የቆጠበ
ለእግዚአብሔር ልቡን የሰበረ
ምኞቱን የረታ ለይቅርታ
ስራዉ ከክብሩ ያላነሰ
ትህትናውን ከዝናው ያልቀነሰ
በሀጥኣን መንገድ የማይሔድ
በፈተና ብዛት የማይታወክ
ዘወትር ክርስቲያን በማንነቱ
ክሷት የወንጌል ሰው በህይወቱ
ለእግዚአብሔር መንግስት የእምነት ሯጭ
ለሰማዕትነት ክብር የሚታጭ
ደግሞስ ሰለ እግዚአብሔር የሚናገር
የት አለ አሱ? የት አገር?

ይቅር ማለት የወደደ
በሰውና ሀጥያት ያልፈረደ
የመንፈስን ፍሬ ያፈራ
ቤቱን አለት ላይ የሰራ
ትዕዛዛቱን ጠብቆ የቆየ
ወንጌል ትርጉም የለየ
ስጋዊ ሀሴት ያልሻረው
በሀሰት ቃል ያልመሰከረው
በልቡ ፍቅር ያሳደረ
ከሰነፎች ጋር ያላበረ
እስከ መስቀል ባለመውደቅ የተጓዘ
ያልቀላቀለ የዕምነት ክብሩን እንደያዘ
ለሰማይ ቤት ስንቅን ያሰናዳ
እጆቹን በሀሰት ያልከነዳ
ማነው ቃሉን የተረዳ?

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን !!
@kinexebebe
2.1K views10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 13:48:15 https://t.me/webzema
1.6K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ