Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ kinexebebe — መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ kinexebebe — መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @kinexebebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.36K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ ኪነ ጥበብ ብቻ የሚገኝበት ቻናል ነው፡፡
ግጥሞች
መነባነቦች
ከዚያም ከዚህ
እናስተዋውቃችሁ
፡ ጭውውት
ድራማ.... ወዘተ
ለሀሳብ @ty1921 ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-09 00:00:01 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች
ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን
በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን
ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን
ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል
ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው
የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው
ቁርባን ቆርበን ሕልመ ሌሊት እንዳይጸናወተን ምን ማድረግ አለብን

በእነዚህ ትምህርቶች ዙርያ እየተማማርን እንገኛለን እርሶም እውቀቱ እንዲኖርዎ ከፈለጉ ይህን መስፈንጠርያ ይንኩ


█▓▒░► 𝑶𝑷𝑬𝑵 ░ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ▒▓█
█▓▒░► 𝑶𝑷𝑬𝑵 ░ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ▒▓█
█▓▒░ ► 𝑶𝑷𝑬𝑵 ░ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ▒▓█
█▓▒░► 𝑶𝑷𝑬𝑵 ░ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ▒▓█

𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር
ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን
ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ በPDF
ኦርቶዶክሳዊ ግጥም
የግእዝ ትምህርት
𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 ‌‌
17 views21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 22:21:26 አንዴ ብቻ ይንኩት አለማትን የፈጠረውን ጌታ
በሕይወት ያመስግኑ ፣ ስትነኩት የሚወስዳችሁ
ቦታ በጣም ይጠቅማቹሀል!

.            ✦              ‍ ‍ ‍ ‍                  ,    

.             .   ゚     .                    .           .            

 ˚                     ゚     .               .      ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ,                * .                    .           ✦           ˚              *                      .  

.             .   ゚     .             .

      ,       .                                                              *         .           .             .                                                               ✦      ,         *          ,    ‍ ‍ ‍ ‍               .            .                                   ˚          ,                              .                 

         

             *          ✦                                .                  .        .        .                .           .            

 ˚                     ゚     .               .
80 views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 11:18:06

1.0K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 09:55:35 *"የህይወት ስንቅ"*


አንድ ወጣት አንድን ታላቅ አባት ጥሩ
ሰው የሚባለው ምን የሚያደርግ ነው ብሎ ቢጠይቃቸው፤
:
*እኚህ ትልቅ አባትም መልሰው ይኸውልህ ልጄ አንተም ብትሆን ጥሩ ሰው ለመሆን ከፈለግክ ሊኖሩህ የሚገቡ ጉዳዮችን ላስቀምጥልህ ልብ ብለህ አድምጠኝ!!*
:
:::---::::---::::---::::---::::
1. "ፈጣሪን የሚፈራ ልብ ይኑርህ!"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ጥሩ ሰው ማለት ፡-
:
~►ዘወትር ለኃጢአቱ የሚጨነቅና ይቅርታ የሚጠይቅ፤

~►ዘወትር በሥራና በትጋት የተጠመደ፤

~►ከመናገር ዝምታን ገንዘብ
የሚያደርግ፤

~►የፈጣሪን ትእዛዛቱን የሚጠብቅና እራሱን ዝቅ የሚያደርግ ነው በማለት መለሱለት፡፡
:
ዓሣ ከውኃ ወጥቶ ከቆየ ወዲያው እንደሚሞት ሰውም ከመንፈሳዊ ሕይወቱ ከወጣ እንደዚሁ ይሞታል፡፡

ዓሣው ቶሎ ተምልሶ ወደ
ውኃው ሲገባ እንደሚድን ሰውም በንስሐ ቶሎ ሲመለስ ፈጣሪ የይቅርታውን በር ይከፍትለታል፤

ስለዚህ ንስሐን እንደ ቀላል ነገር አትቁጠረው፤

2 ." መልካምነት ውደድ !"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ከተሰወረ ፍቅር የተገለጠ ዘለፋ፣ ከጠላት መልካም ሐሳብ የወዳጅ ክፉ ምክር፣ ከራቀ ወንድም የቀረበ ወዳጅ ሳይሻል እንደማይቀር አትዘንጋ፤

መልካም ሞት የመልካም ኑሮ ውጤት ነው፤

አንደበተ ትልቅ ውስጠ ቀላል እንዳትሆን ተጠንቀቅ

3. "በፈጣሪ እንጂ በደጋፊዎች አትተማመን!"
:::---::::---::::---::::---::::

በደጋፊዎች ከተማመንክ ከሰባራ ወንበር ላይ እንደተቀመጥክ ቁጠረው፤

የሰይጣን ደህና ባይኖረውም፣ ብቻውን ካለ ሰይጣን ይልቅ በሰው ላይ ባደረ ሰይጣን ተጠንቀቅ፣ በሰው ላይ ያደረ ሰይጣን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ስትለው ከሰውየው ጋር ተጣብቆ ያስቸግራልና፡፡

4 ."ካለፈው ስህተትህ ተማርበት እንጂ አትማረርበት!"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ሰዎች በአንተ ላይ ምንም እንዳያወሩ ሥልጣን የለህምና፤ የሚሉህን እየሰማህ ስህተትህን አስተካክል፤
:
5 ."አስፍቶ መረዳትን አዳብር!"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ሌሎች እንዴት ማጥቃት እንዳለብህ
የሚነግርህን ሰው ሌላ ጊዜ እሱ ሲያጠቃህ እንዴት መካለከል እንዳለብህ እየነገረህ እንደሆነ ተረዳው።
:
ሌሎችን ቀርበህ እንዴት እንደምትወድ የሚነግርህን ሰው ግን ለፍቅር እድል ስጠው።
:
6 ." ለመታመን ማመን አለብህ!"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ሰውን ማመን ቀብሮ ነው የሚለው አስተሳሰብ ስህተት ነው።
:
ለማመን ሰው መቅበር ካስፈለገ
የተቀበረን ለማመንም መቀበር ሊያስፈልግ ነው።
:
ሰውን የማምነው ቀብሬ ከሆነ ሌሎችም እኔን የሚያምኑኝ ቀብረውኝ ነው።
:
መኖር ግዴታ በሆነበት ህይወት ውስጥ ሞት መብት አይሆንም።
:
ማንኛውም ሰው ራሱን በህይወት ማቆየት እንጂ ለመሞት ራሱን መግደል አይችልም።
:
ነገር ግን ራስን ለመግደል ቀላል ዘዴ አለ። :
►መጀመሪያ ማሳብ ማቆም።
:
►ቀጥሎ ማሰብ ያቆምከውን አሳብ መኖር።
:
7. "ለማድረግ ተዘጋጅ!"
:::---::::---::::---::::---::::
:
ለማድረግ ስታስብ እጥፍ አድርገህ አስብ!"
:
ያሰብከውን ስትተገብር በቁመትህ ልክ አድርግ።
:
ከፍ ባልክ ቁጥር ከፍታህ ቋሚ መድረሻህ አለመሆኑን እወቅ።
:
ወደ ላይ ከፍ ስትል ወደ ታች ተመልከት።
:
በከፍታህ ወቅት ወደታች መመልከትህ ስትወድቅ የምታርፍበትን ምቹ ቦታ እንድትለይ ያደርግሀል።
:
8. "ለችግር የተሸነፍክ አትሁን !"
:::---:::::---::::---::::---:::::
:
በህይወትህ ችግር ሲያጋጥምህ ችግሩን መለየት የመፍትሄ መጀመሪያ መሆኑን ተረዳ።
:
ችግሩን የመለየት መጀመሪያው ደግሞ አንተ ራስህ በራስህ ችግር አለመሆንህ ለይቶ ማረጋገጥ ነው።
:
ሳያልፍ የመጣ ክፉ ነገር የለምና እስኪያልፍ ታገሥ፤

9 ."ትንሽ ለመስጠት አትፍራ !"
:::---::::---::::---::::---::::
:
የስጦታ ዋጋ በተቀባዩ ስሜት እንጂ በስጦታው ይዘት አይወሰንም።
:
ለሰጪው ትንሽ የሆነ ለተቀባዩ ትልቅ ዋጋ አለው።
:
10. "ክብርህን ከምግባርህ እንጂ ከሰው አትጠብቅ !"
:::---::::---::::---::::---::::
:
የምትቀበለው አንተ አስቀድመህ በሰጠኸው ልክ ነውና!
:
ለመከበር ፤ ለመወደድ ፤ ጥሩ ጓደኛ ለማግኘት አንተ አስቀድመህ ሌሎቹን አክብር ፤ ውደድ ፤ጥሩ ጓደኛም ሁንላቸው ምክንያቱም መልካምነት ለራስ ነውና!
:
በህይወታችን ለሰዎች ከክፋት የነጻ
በፍጹም ንጹሕ ልቦና መልካምና ቅን ሆነን እንኖር ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን!

@kinexebebe
2.2K views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 13:43:19 ላለማመን ወስኖ ከመጣ ሰው ጋር አትከራከር
፨፨
በተለያዩ ጉዳዮች ሃይማኖትን ጨምሮ ሐሳባችን ስንገልጽ/ስንወያይ  ልዩነት ሊኖር ይችላል
አንዳንድ ሰዎች ከራሳቸው ሐሳብ ውጪ ምንም ያህል ማስረጃ ብታቀርብ አይቀበሉትም። ይህ ሰው ላለማመን ወስኖ ስለመጣ ከእርሱ ላይ ጊዜ መጨረስ አያስፈልግም።

ላለማመን ወስኖ የመጣ መሆኑን በምን ታውቃለህ የሚል ሰው ይኖራል
1ኛ ሲናገር ጮክ ብሎ /በቁጣም ሊሆን ይችላል  ይሆናል።
2. እርሱን ሊያሸንፍ በሚችል በማስረጃ እየተናገርክ እየገባው እያለ unconciously /ሳያስበው ንግግርህን ያቋርጥሃል
3. ከርዕሱ ወይም ጭብጡ ውጭ ያወራል።

ይህ ሰው ለምን ላለማመን ወስኖ  ይመጣል? የሚል ሰውም ይኖራል።
ይሄ ከባድ ጥያቄ ነው ነገር ግን መልስ አይጠፋውም
ምክንያቱ
1) ይህ ሰው ሃሳቡን እንደ ዶግማ/የማይለወጥ አድርጎ ይዞታል ያን ዶግማ ሊሸረሽር የሚችል ነገር አይቀበልም።
2) ከግል ስብዕናው ጋር የተያያዘ ችግር ሊሆን ይችላል
3) ሀሳብክን በህሊናው ሊቀበል ይችላል ነገር ግን ተሸነፈ ላለመባል ብቻ በቃል ደረጃ የማይቀበል ሊሆን ይችላል። ስለዚህም እንደማንም ብሎ የሰማውን ሐሳብ suppress/በጭንቅላቱ ሊደብቀው ብሎም ረፍት ስለሚነሳው ለመርሳት ይሞክራል።
ባጠቃላይ ይህ ሰው የሚቀበለው እውነቱን ሳይሆን እርሱ እውነት እንዲሆን የሚፈልገውን ነገር ነው ።
ምንም ያክል ልዩነት ቢኖርም  ክርክሩን መተውና ልዩነትን መቀበል እንጅ በእርሱ ላይ መፍረድ አያስፈልግም
@kinexebebe
1.8K views10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 13:37:44
በሀገረ እግዚአብሔር / በቅድስት ምድር /
በእመቤታችን ርስተ ምድር በሆነችው በኢትዮጵያ የሰው ልጅ ደም እየፈሰሰ ነው ፡፡
ኢትዮጵያ ሹሙ እንደ ጠፋበት ንብ ህዝቡ ከተበታተነ ሰነበተ። የሰው ሕይወት የውሻ ሕይወት ያክል ተቆጥሮባታል ፡፡
አምላክ ከ 22ቱ ፍጥረታት ለይቶ አምላካዊ ክብሩን
የሰጠው የሰው ፍጡር እየሞተም እየገደለም ነው ፡፡ ሰው ሠውን እያደነ ነው ፡፡
ከሰው ሕይወት ይልቅ ስንዝር መሬት ትልቅ ከበሬታ አግንታለች። ሁሉም ነገ ጥሎት ለሚሄድ መሬት እየተስገበገበ ነው። በዚች ሀገር የጥይት
ባሩድ እየሸተተ ነው ፡፡ ህዝቡ ደስታውን ሳያጣጥም ጥቁር ደመና እየመጣበት ነው ፡፡ በዚች ሀገር ፈሪሀ እግዚአብሔር ያለው አስታራቂ ሽማግሌ ይፈለጋል፡፡
ቅዱሳን የመነኑበት ምድር በእግዚአብሔር ቁጣ እንደ እስራኤላውያን ቤተ መቅደስ እንዳትሆን እንፈራለን፣የሙሴ ጽላት ያለባት ምድር የሶረያን እጣ እንዳታገኝ እንፈራለን። ምንግዜም ሰው ሲያጠፋ ሀገር ባድማ ትሆናለች፡፡
በፈረሱ የተማመነ ይጠፋል ይላል ነብዩ ዳዊት።
የፈርዖን ታሪክ እንዳይደገም እንፈራለን ፡፡ የሰው ደም ከባድ ነው። ትልቅ መከራ ያስከፍላል ፡፡ ሳጥናኤል ክፉ
ነው። ከላይ ከትዕቢት ተራራ ላይ ሰቅሎ ወደ ውርደት ሸለቆ ይፈጠፍጣል፡፡
ምን ይሁን ኢትዮጲያውያን እርስ
በርስ አዳኝና ታዳኝ ሆነው በደማቸው ይራጫሉ ፡፡
አንደበቱ ቅባ ቅዱስ የተቀባ መሪ እቺ ሃገር ትፈልጋለች።
@kinexebebe
1.6K viewsedited  10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 12:51:05 #አረ_ጉድ_ነው አሁን_ደሞ_ምን_ተጀመረ_አሁኑኑ_ይህን_ቻናል_join_ይበሉና_ጉድ ይመልከቱ
1.3K views09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 13:31:50 ( የንስሐ ግጥም ! )

አባ ስማ ድምፄን ደጅህ ቆሚያለሁኝ
የጠፋሁት ልጅህ በር እየመታሁኝ
በሀፍረት ታጥሬ እንደተሸማቀቅኩ
በፀፀት ታጅቤ እንደተኮራመትኩ
ከናፈቅኩት ቤትህ አይኔን እያማተርኩ
ቁጭ ብያለሁ ደጅህ አንተን እየጠበኩ
አባ ተመልከተኝ እንዲህ ተጎድቼ
የልጅነት መልኬን ወዜን ሁሉ አጥቼ
ካንተ የተቀበልኩት ጥሪቴን አጥፍቼ
በዚህች ወረተኛ አለም ተከድቼ
አዎን መጥቻለው ጉስቁልቁል እንዳልኩኝ
እርቃኔን ሳልሸፍን እንደተራቆትኩኝ
የህሊና እስረኛ መንገድ የጠፋብኝ
ሆኜ ቀርቻለው አለም ተጫውታብኝ
አባ ያንን ጊዜ ካንተ እንደተለየው
የዝ'ችን አለምን ጉድ ስንት ነገር አየው
ለካንስ እውነት ነው ምድር ከንቱነቷ
አያልቅም ተወርቶ ኮተታኮተቷ
አሳስቃ ወስዳ እያታለለችኝ
ይኸው አንገዋላ ከመንገድ ጣለችኝ
የምሸሸግበት ማርፍበት እስካጣ
ወዳጅ ተለውጦ እስኪሆን ባላንጣ
አይመስለኝም ነበር የጭካኔዋ ጥግ
አላስተዋልኳትም ያሻትን ስታደርግ
በርሀብ እና በጥም እየተሰቃየው
መሄድ እስኪያቅተኝ እየተንገላታው
የችግሬን ዳገት ብቻዬን ስገፋው
አልደረሰልኝም ወዳጅ ያልኩትም ስው
ግን ጥርሴን ነክሼ ሰው ለመሆን ዳግም
ስቃይ ያደቀቀው ማንነቴን ላክም
በጉልበቴ ድኼ እንዲያ ስፍገመገም
ያን ጊዜ አየሁት ፊት ለፊቴ ሲቆም
ትንሿን ተስፋዬን ድጋሜ ሊያጨልም
ለካን ውሸት ኖሯል ፍቅራችን የይምሰል
ለካን ለጌጥ ሆኗል የለበስነው መስቀል
ይሄኔ ነው ታዲያ ልቤ ቤትህን ናፍቆ
ይቅርታ ሊጠይቅ ከእግሮችህ ስር ወድቆ
የመጣው በድፍረት ተስፋውን ሰንቆ
አባ አደራህን እንዳትጨክንብኝ
በርህን ለመክፈት እንዳትዘገይብኝ
በመከራ ምክር  በጣም ስለደከምኩ
መኖር መርጫለው ለአንተ እያገለገልኩ
እንጂማ ከእንግዲህ ሌላም እቅድ የለኝ
አባ ቶሎ መተህ እንዳረከኝ አርገኝ
ወዲህ ወዲያም ሳልል ቆሚያለው በርህ ላይ
በይቅርታ አይኖችህ ዳግም እስከምታይ
ፈራ ተባ እሚለው ልቤን እየሞገትኩ
እስካሁን በርህ ለይ እንደተኮራመትኩ
ቁጭ ብያለው እና አንተን እየጠበኩ
አባ ናልኝ ባክህ ኧረ እኔስ ተጨነኩ
አንዴ ብቻ መተህ በሩን ከፍተህ ካየህ
በልጅህ መሰበር ስንቱን ታስባለህ
ግን አንድ እውነት እውቅ ከመምጣትህ በፊት
በርህን ደብድቤ ብጣራም በድንገት
አጥፍቼው ብመጣም ያንን ሁሉ ንብረት
ገንዘብ የማይገዛው ልብን ገዝቻለው
ከትናንቱ ግብሬ ዛሬ ተሽያለው
ስለዚህ ስትመጣ በሩን ልትከፍትልኝ
በዛሬ እኔነቴ እንድትቀበለኝ
ከቤት አስገብተህ አገልጋይህ አድርገኝ
ልጅህ ልባል እንደው አልሻም ከ'ንግዲህ
አገልጋይህ ሆኜ ልሩጥ ወዲያ ወዲህ
አዎን አባ መጥተህ በሩን ስትከፍትልኝ
አልሻም ድጋሜ
የአባትነት ዋጋን እንድትከፍልልኝ
ከቤታችን ካሉት ከአገልጋዮች ጋራ
እንድትፈቅድልኝ አብሬ እንድስራ
እለምንሀለው እሺ በለኝ  ባክህ
ያንን የትናንቱን ደጉን ቀን አስብህ
እንጂማ እንደግብሬ እንደ'ኔማ ቢሆን
አንተን ባለፈለኩህ ወዳጁ አውሬ ሲሆን
በቃኝ ስልችቶኛል ደክሞኛል እንግልት
በደንብ ገብቶኛል የምድር ከንቱንት
ላልመልሰው ፊቴን እርም ይሁን ብያለው
ቤትህ ነው አለሜ አባ ተምሪያለው!!!

ለሁላችንም መሃሪ ይቅር ባይ አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለንስሐ ሞት ያበቃን አሜን !!
@kinexebebe
2.6K views10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 09:49:40 ፨የአፎምያ አጽናኝ፨





ከቀደመው መንገድ ከላይ በተሰጠን
ዕድሳት በማያውቅ በማይሻርው ዘመን
በድንቅ ምስክሮች ብርሃን በሆኑን
እንድንጓዝ ሁሌም የአፎምያ አጽናኝ
ጠላት ቀስቱን ሰብቆ ሊያጠፋን ሲመጣ
እንደ ቋጥኝ ከቦን የዚህ አለም ጣጣ
በከንቱ ስንሮጥ ኋላ እንዳንቀጣ
አማልደን መላኩ የነፍሳችን ዕጣ
የሁሉንም ጸሎት ከአምላክ የምታደርስ
ፍቅር እና ርህራሄ በሰው የምታለብስ
ልክ እንደ ትላንቱ ዛሬም ፈጥነህ ድረስ
በአንደበትህ ፍሬ ውስጣችን ይታደስ
የዳንኤል አጽናኝ የአፎምያ ረዳት
በህይወት የቀየርክ የባህራንን ጽሕፈት
በለአምን የታደክ ከእርግማን መቅጸፍት
እኛንም ጠብቀን ከምናየው መአት
የምጽአት ዋዜማ ለመሆኑ ምስክር
በመጽሐፍ ያለው ቃሉ ሲተገበር
መተማመን ጠፍቶ ሲቀዘቅዝ ፍቅር
በወንጌሉ አንድምታ ልባችን ይታጠር
ይቅርታ ምህርቱ ይምጣልን የእግዚአብሔር
እረኛ እንደሌለው ሲጨነቅ ትውልዱ
ተመሳስሎ ቆሞ ሲያስት በመንገዱ
ግራ በመጋት ስንቶቹ ተጎዱ
በየዋህነታቸው አብረው ተሰደዱ
ዘንዶ አፉን ከፍቶ ነፍሳት እንዳይወጥ
የተዋህዶን መዝገብ እውነቱን ለመግለጥ
የቆመውን ሁሉ በአውደ ምህረቱ
ያበረታን አምላክ እሰከ ምጽአቱ።


እንኳን ለሊቀመላአኩ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ የንግስ ክብር በዓል በሰላም አደርሳቹ አደረሰን የመላአኩ ረድኤት እና ምልጃው አይለየን አሜን!
@kinexebebe
2.1K views06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 10:17:51 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን(፫)

"የማለዳ ፆለት"
የጊዚያት ባለቤት እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ
የጨለማዉን ግርማ ገፈህ
ብርሀንን እንድመለከት
ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ።
በምኝታየ ስለጠበከኝ ከሞት
ስለሰወርከኝ እጅ መንሳቴን
አቀርባለሁ።
ቸር እረኛየ ትጉህ የማታንቀላፋ ነህና ለሊቱን ከ እኔ ጋር ሁነህ እደጠበከኝ
ይህንንም ማለዳ ባርከህ ቀድሰህ የሰላም ዉሎ እንድዉል ቀኝህ ትርዳኝ።
መንገዴን ሁሉ ከፊት እየሆንክ ምራኝ።
ከደካማ ፍጡርነቴ የተነሳ
በኃላየ ምን ምን እንዳለ
አላዉቅምና አንተ ጠብቀኝ።
በዙሪያየ ሁሉ ጠላት ያስቀመጠብኝን እንቅፋትና መሰናክል አስወግድልኝ።
ከፈተና የተነሳ ብወድቅ እንኳን አንሳኝ እንጅ አትተወኝ።
በዚእች ቡርእክት እለትም
በስራየ፣በንግዴ በመንገዴ፣
በክብሬ፣በአገልግሎቴ ሁሉ
የጥፋት መረቡን ዘርግቴ
ሰላሜንና በረከቴን ሊያሳጣኝ
የተዘጋጀዉንና የሚያሴርብኝን
ጠላቴን(ዲያቢሎስን)እቅድና
ስራዉን አፍርሰህ ሰላሜን
አጎናፅፈኝ።
በዚህ እለት ሀጢያትን አቅጀ
በድፍረት እንዳልፈፅም በመዘናጋትም እንዳልተገብር
አድርገኝ።
ደም ከሚፈስበት ፍርድ ከሚዛባበት ድሀ ከሚበደልበት በማታለልና በማጭበርበር ከሚከበርበት
ጣኦትና ሰይጣን ከሚመለክበት ስራና ቦታ ሁሉ
ፈፅመህ ጠብቀኝ።
ደካማዉ ልጅህ እጆቸን ዘርግቸ መንገዴን እንድትመራኝ በቀረቡህ ጊዜ
ሀጢያቴንና በደሌን አይተህ
ሳትጠየፈኝ ተቀብለህ ምራኝ።
እለቱን ሁሉ ፍቃድህን ማድረግ እንድችል በቃልህ
አስተምረኝ።
መንፈስ ቅዱስ ሂወቴን ይቆጣጠር።
ትናንትን እንደጠበከኝ እንደ መገብከኝ ከክፉም እንደሰወርከኝና እንደ ፈወስከኝ ዛሬም እንደ ፈቃድህ ጠብቀኝ።
አንተ ያልከዉ ይሆን ዘንድ ግድ ነዉና በከንቱ ከመጨነቅና ተስፋ ከመቁረጥ ሰዉረኝ
ለዘልአለሙ


አሜን አሜን አሜን
@kinexebebe
1.9K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ