Get Mystery Box with random crypto!

✞✞✞ ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞✞✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ kidusan_z_ethiopia — ✞✞✞ ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞✞✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ kidusan_z_ethiopia — ✞✞✞ ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞✞✞
የሰርጥ አድራሻ: @kidusan_z_ethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.02K
የሰርጥ መግለጫ

✞ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞
♦♦♦ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን♦♦♦
❇ የዚህ ቻነል አላማ ❇
▶ ▶ ▶ ከኢትዮጵያ የተገኙ የቅዱሳን አበው እመውን (አባቶች እና እናቶች) የቅዱሳንን ስም ፡ የተጋድሎ ህይወት ፡ ፍሬ በጥቂቱ ማስተላለፍ ማስተማር ነው፡
➕ የቅዱሳን <ቅድስና>የብፅዕና የቅድስና ተጋድሎ ታሪክ ገድል ቃልኪዳን እንገብይ እንምሰላቸውም፡፡
ዕብ ፲፫÷፯-፱
@kidusan_Z_ethiopia

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-11-21 01:20:50 በኢትዮጵያ የተሰወሩ ፒራሚዶች ያሉበት ቦታ ታወቀ !



እነዚህ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች የሚገለጡበት ዘመን ታወቀ


እውነት በኢትዮጵያ መሬት በሰማያዊ ሀይል ተቀብረው የሚገኙ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች አሉ ? እንዴትስ ተሰሩ ?

ስለ እነዚህ ፒራሚዶችና ቤተመቅደሶች አስገራሚ ምስጢሮች


በቅዱሳን አባቶቻችን ስለተሰወረው ድንቅ መፅሐፍ


እነዚህን እና ሌሎች ሚስጢራትን ስለ ኢትዮጵያ ስውር ቤተ መቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ማወቅ ከፈለጉ በ Youtube ቻናላችን ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት ትችላላቹ ከስር ያለውን Open የሚለውን ተጭነው ! እንዲሁም ሌሎች ድንቅ ፕሮግራሞችንም ማግኘት ይችላሉ በዛውም የ Youtube ቻናላችንንም Subscribe ያርጉ !




ይህን ይጫኑት ... ይህን ይጫኑት
.
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
979 viewsመንፈሳዊ 0K, 22:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-07 23:01:15 በኢትዮጵያ የተሰወሩ ፒራሚዶች ያሉበት ቦታ ታወቀ !



እነዚህ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች የሚገለጡበት ዘመን ታወቀ


እውነት በኢትዮጵያ መሬት በሰማያዊ ሀይል ተቀብረው የሚገኙ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች አሉ ? እንዴትስ ተሰሩ ?

ስለ እነዚህ ፒራሚዶችና ቤተመቅደሶች አስገራሚ ምስጢሮች


በቅዱሳን አባቶቻችን ስለተሰወረው ድንቅ መፅሐፍ


እነዚህን እና ሌሎች ሚስጢራትን ስለ ኢትዮጵያ ስውር ቤተ መቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ማወቅ ከፈለጉ በ Youtube ቻናላችን ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት ትችላላቹ ከስር ያለውን Open የሚለውን ተጭነው ! እንዲሁም ሌሎች ድንቅ ፕሮግራሞችንም ማግኘት ይችላሉ በዛውም የ Youtube ቻናላችንንም Subscribe ያርጉ !




ይህን ይጫኑት ... ይህን ይጫኑት
.
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
1.1K viewsመንፈሳዊ 0K, 20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-10 04:55:12 በኢትዮጵያ የተሰወሩ ፒራሚዶች ያሉበት ቦታ ታወቀ !



እነዚህ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች የሚገለጡበት ዘመን ታወቀ


እውነት በኢትዮጵያ መሬት በሰማያዊ ሀይል ተቀብረው የሚገኙ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች አሉ ? እንዴትስ ተሰሩ ?


ስለ እነዚህ ፒራሚዶችና ቤተመቅደሶች አስገራሚ ምስጢሮች


በቅዱሳን አባቶቻችን ስለተሰወረው ድንቅ መፅሐፍ


እነዚህን እና ሌሎች ሚስጢራትን ስለ ኢትዮጵያ ስውር ቤተ መቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ማወቅ ከፈለጉ በ Youtube ቻናላችን ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት ትችላላቹ ከስር ያለውን Open የሚለውን ተጭነው ! እንዲሁም ሌሎች ድንቅ ፕሮግራሞችንም ማግኘት ይችላሉ በዛውም የ Youtube ቻናላችንንም Subscribe ያርጉ !




ይህን ይጫኑት ... ይህን ይጫኑት
.
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█



.
1.9K viewsመንፈሳዊ 0K, 01:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-10 10:31:41 + ያደረግሽው ምንድር ነው? +

አዳም ዕፀ በለስን በበላና ክብሩን ባጣ ጊዜ እግዚአብሔር ሲጠይቀው እንዲህ አለ :- ከእኔ ጋር እንድትሆን የሠጠኸኝ ሴት ከዛፉ ሠጠችኝና በላሁ::

ከዚያ በኁዋላ ግን እግዚአብሔር ለሔዋን :- ለምን ዛፉን ብላ ብለሽ ሠጠሽው? አላላትም:: "ያደረግሽው ምንድነው" ብቻ አላት::

እርሱ በሰዎች አስተያየት አይፈርድም:: ሌላው ስለ አንተ የሚለውን ትቶ አንተን ለብቻህ ይጠይቅሃል:: የሰዎችን ግምገማ አይሰማም:: እንደ ሃናንያ "ኸረ ጌታ ሆይ ክርስቲያኖችን ሲያሳድድ ነበረኮ" ቢሉትም ቸል ብሎ ምርጥ ዕቃው ያደርግሃል:: በድንጋይ ልትወገር ይገባታል ሲሉት ክሱን ትቶ ከሳሾቹን ሊከስስ መሬት ላይ ይጽፋል::
ዐሥርቱ ትእዛዛትን በጻፉ ጣቶቹ ዘማዊትዋን ሴት ነጻ ሊያወጣ አፈር ይጭራል::

ሰው ጨካኝ ፈራጅ እንደሆነ ያውቃልና በአዳም አስተያየት ሔዋን ላይ አይፈርድም:: "ያደረግሽው ምንድን ነው?" ብሎ ጠየቃት::

እግዚአብሔር ዛሬም ነፍሳችንን ይጠይቃታል::

ያደረግሽው ምንድር ነው? የአዳምን ክስ ሰምቻለሁ! ሰዎች ስለ አንቺ የሚሉትን አዳምጫለሁ:: አንቺ ግን ንገሪኝ:: ግራውን ሰምቼ አልፈርድም:: ምናልባት ቀኙን ብሰማ ይሻላል የሚል ርኅሩኅ አምላክ ነው::
እኛ የምንፈርድባቸው ሰዎች ሁሉ ቢጠየቁ የሚናገሩት የየራሳቸው የታሪክ ማዕዘን (side of the story) አላቸው::
ስለዚህ እግዚአብሔር አዳምን ሰምቶ አልፈረደም ሔዋንን ጠርቶ ጠየቃት
"ያደረግሽው ምንድር ነው?"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
4.3K viewsYadesa Damena, 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-09 05:42:21 እመቤታችን ተወለደች ማለት ጌታ ሊወለድ 15 ዓመት ቀረው ማለት ነው:: እግዚአብሔር ከሴት የተወለደ ልጁን ሊልክ የዘመኑ ፍጻሜ ቀረበ ማለት ነበር። እግዚአብሔር ሃና እና ኢያቄምን ሳይወልዱ ያዘገያቸውም ለዚህ ታላቅ ክብር እንዲበቁ ነበር።
ቀድመው ልጅ ቢወልዱ ኖሮ ይህችን የፍጥረት ደስታ የሆነች ልጅ አይወልዱም ነበር:: የእርስዋ የልደት ቀን የፍጥረት ደስታ ቀን ነው::

ክርስቶስ ፀሐይ ከሆነ የዛሬው ዕለት ሰማይዋ የተዘረጋችበት ዕለት ነው።

ክርስቶስ የሕይወት ውኃ ከሆነ ዛሬ ምንጭዋ የፈለቀችበት ዕለት ነው።

ክርስቶስ መድኃኒት ከሆነ ዛሬ የመድኃኒቱ ሙዳይ የተገኘችበት ዕለት ነው::

ወንጌል በመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ይላል። በእመቤታችን መወለድ ምን ያህል ሰዎች ደስ ይላቸው ይሆን? የእመቤታችን ልደት በብዙ ሀገራት ብሔራዊ በዓል ሆኖ ይከበራል።

እኛም በሊባኖስ ተራሮች (አድባረ ሊባኖስ) መወለድዋን በማሰብ ከደጅ ወጥተን ቅድም አያቶችዋ በጨረቃ ተመስላ በህልማቸው ያዩአትን የጨረቃችንን (በግሪኩ ሶልያና) ልደት ጨረቃን እያየን እናከብራለን። የልደትዋ ቀን ልደታችን ነው!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት ልደታ 2012 ዓ ም
3.6K viewsYadesa Damena, 02:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 14:00:47 + የሰጠኸኝ ሴት +

እግዚአብሔር አዳምን "አትብላ ካልሁህ ዛፍ በላህን?" ብሎ ጠየቀው:: አዳምም :- ከእኔ ጋር እንድትሆን የሠጠኸኝ ሴት ከዛፉ ሠጠችኝና በላሁ አለ::

የሰጠኸኝ ሴት! በጣም ይገርማል:: ሚስቴ አላለም::
አዳምና ሔዋን የተገናኙ ቀን አዳም ያለውን አስታውሱ
"ይህች አጥንት ከአጥንቴ
ይህች ሥጋ ከሥጋዬ" ብሎአት ነበር::
ምንም እንክዋን አዳም ወላጆች ባይኖሩትም ሰው እናትና አባቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ብሎም ነበር::
ራቁታቸውን ቢሆኑም አይተፋፈሩም ነበር::

አሁን በራቁቱ ብቻ ሳይሆን በሔዋንም አፈረባት::
እናትና አባቱን ይተዋል እንዳላለ ሔዋንን ራስዋን ተዋት::
ከሚስቱ ጋር መተባበር ቀርቶ ክስ ጀመረ::

አካሌ አጥንቴ ሥጋዬ ማለቱ ቀረና የሠጠኸኝ ሴት አለ::
የጫጉላው ጊዜ አለፈና ከሚስትነትዋ ሴትነትዋ ብቻ ታየው::

በጋብቻ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር የሠጠንን ነገር
ሁሉ ቀድመን የራሳችን እናደርጋለን ነገሮች ሲበላሹ ግን ባለቤትነቱን ወደ እርሱ እንመልሰዋለን::

የሠጠኸኝ ሥራ
የሠጠኸኝ ወላጆች
የሠጠኸኝ ሰፈር
የሠጠኸኝ ሀገር
የሠጠኸኝ መሪ
የሠጠኸኝ ጉዋደኞች
የሠጠኸኝ ደካማ ሥጋ
የሠጠኸኝ ዓይን

ትናንት ሲሠጠን ዘምረን የተቀበልነውን ሥጦታ ዛሬ ለምሬት እንጠቅሰዋለን:: የሠጠኸኝ የሠጠኸኝ .... ሠጠኝና በላሁ ብለን ቀርጥፈን ለበላነው ዕፀ በለስ ፈጣሪን እንከስሰዋለን::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
5.1K viewsYadesa Damena, edited  11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-12 08:51:02 አባ ሕርያቆስ
(ዲ. ሕሊና በለለጠ)
+++++++++
ጥቅምት ኹለት የአባታችን የአባ ሕርያቆስ ዕረፍቱ ነው፡፡ አባ ሕርያቆስ ከጽድቅ ሕይወቱ ባሻገር ለእመቤታችን ባለው ፍቅርና በደረሰው የቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ የሚታወቅ ታላቅ አባት ነው፡፡ በ1994 ዓ.ም. ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ያሳተመው (አዲስ አበባ) ስንክሳር የጥቅምት ኹለቱ ንባብ “ወበዛቲ ዕለት … ተዝካሮሙ ለሕርያቆስ ወቴክላ ሰማዕት በረከቶሙ ተሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን” (ትርጉም- በዚህችም ቀን ደግሞ የሕርያቆስና የሰማዕት ቴክላ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን፡፡) ከማለት በስተቀር የሚገልፀው ነገር የለም፡፡ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜን የመሳሰሉት መጻሕፍት ግን ስለ ጻድቁ በጥቂቱ ያትታሉ፡፡

-----የስሙ ትርጓሜ

ሕርያቆስ/ ኅርያቆስ ማለት (የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ) እንደሚገልጠው ኅሩይ/ምርጥ/ ማለት ነው፤ ለሹመት መርጠውታልና ምርጥ ተባለ፡፡
አንድም ረቂቅ ማለት ነው፤ ምሥጢረ ሥላሴን ከኹሉ ይልቅ አምልቶ አስፍቶ ይናገራልና፡፡
አንድም ፀሐይ ማለት ነው፤ አብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ እያለ ጽፏልና፡፡
አንድም ብርሃን ማለት ነው፤ የምእመናንን ልቡና በትምህርቱ ብሩህ ያደርጋልና፡፡ ዘአብርሃ መንበረ ማርቆስ በብርሃን እንዲል፡፡
አንድም ንህብ ማለት ነው፤ ንህብ የማይቀስመው አበባ የለም፣ እርሱም የማይጠቅሰው ሊቅ የለምና፡፡

--------ሹመት

ሐዋርያት ስለ ሹመት በሠሩት ቀኖና የተማረና ግብረ ገብ የኾነ እንዲሾም አዝዘዋል፡፡ ኹለቱንም ያስተባበረ ባይኖር ግብረ ገብ የኾነ ነገር ግን ያልተማረ እንዲሾም ሥርዓቱ ያዛል፡፡ ትምህርቱን በጊዜ ሂደት ያመጣዋልና፡፡ በዚኽም መሠረት አባ ሕርያቆስ ያልተማረ ቢኾንም በምግባሩ የተመሠከረለት ግብረ ገብ በመኾኑ ተሾመ፡፡ በዚኽ ሹመትና ሥርዓትን የሚያፀና በመኾኑ ግን በክፋት የሚቀኑበት ብዙዎች ነበሩ፡፡ ያልተማረ በመኾኑም ይንቁታል፡፡ ዕለት ዕለትም አዋርደውት ከሹመቱ ለማስሻር ይጥሩ ነበር፡፡ እርሱ ግን “ወእቀውም ዮም በትሕትና ወበፍቅር” እንዲል እንደጠሉኝ ልጥላቸው እንደናቁኝ ልናቃቸው ሳይል በፍቅርና በትሕትና ጸንቶ ያስተምራቸው ነበር፡፡

--------የዕውቀት መገለጥ/የቅዳሴ ማርያም ድርሰት

አባ ሕርያቆስ ተምኔቱ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ የእመቤታችን ምስጋና እንደ ባሕር አሸዋ እንደ ሰማይ ኮከብ በዝቶልኝ፣ እንደ ምግብ ተመግቤው፣ እንደ መጠጥ ጠጥቼው፣ እንደ ልብስ ለብሼው እያለ ይመኝ ነበር፡፡
በእርሱ የሚቀኑበት ተንኮለኞች ከዕለታት በአንዱ ቀን በምን ምክንያት እንሻረው ብለው ተማክረው ቀድሶ ማቁረብ አይችልምና ቀድሰህ አቁርበን ብለን በዚህ ምክንያት እንሻረው ብለው ተስማሙና እንዲቀድስ አደረጉት፡፡
አባ ሕርያቆስም ሥርዓቱን ጨርሶ ከፍሬ ቅዳሴው ሲደርስ ተንኮለኞቹ “ከሊቃውንት ቅዳሴ የሚያስቸግረውን እናውጣለት” እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ የለመኗትን የማትነሳ የነገሯትን የማትረሳ እመቤት ገልጻለት “ጎሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ” ብሎ “ወይእዜኒ ንሰብሖ” እስኪል ድረስ ሰተት አድርጎ ተናግሮታል፡፡
የሚንቁትና የሚጠሉት ሰዎች “ ይኽ የነገሩትን ቀለም እንኳን አከናውኖ መናገር የማይቻለው ዛሬስ እንግዳ ድርሰት እደርሳለሁ ብሎ ያገኘ ያጣውን ይቀባጥር ጀመረ!” ብለው አደነቁበት፤ የሚወዱትና የሚያከብሩት ግን “ከመንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እንዲኽ ያለ ምሥጢር ከእሩቅ ብእሲ ይገኛልን” ብለው አደነቁለት፡፡ ወዲያውም ጽፈን ደጉሰን ልማድ እንያዘው ብለው ወሰኑ፡፡ ተንኮለኞቹ ግን ይኽንንም ስለተቃወሙ እንደ ሀገራችን ልማድ እንያዘው በሚል ተስማሙ፡፡ በሀገራቸው ልማድ እንግዳ ድርሰት የተደረሰ እንደኾነ ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ይጥሉታል፣ ከእሳት ሳይቃጠል የወጣ እንደኾነ ከውሃ ይጥሉታል፣ ከውሃ ሳይርስ የወጣ እንደኾነ ከሕሙም ላይ ይጥሉታል፣ ድውይ የፈወሰ እንደኾነ ደገኛ ድርሰት ነው ብለው ይይዙታል፡፡

ይኽንንም የአባ ሕርያቆስን ድርሰት ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ላይ ጣሉት ከእሳት ሳይቃጠል ወጣ፤ ከውሃ ጣሉት ሳይርስ ወጣ፤ ከሕሙም ላይ ጣሉት ድውይ ፈወሰ፣ ይልቁንም ሙት አስነሣ፡፡ ከዚኽ በኋላ ደገኛ ድርሰት ነው ብለው ጽፈው ደጉሰው ያዙት፡፡ በጥራዝም (ከ13ቱ ቅዳሴያት ጋር) 14ኛ አድርገው ጠርዘውታል፡፡

የተቀደሰው ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት በአንዱ ቀን ነው፡፡ የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ አባ ሕርያቆስ ምሥጢር ባይገለጥለት ኖሮ በዕለቱ ቅዳሴ ሐዋርያትን ወይም ቅዳሴ እግዚእን ይቀድስ እንደነበር ይጠቁመናል፡፡ ቅዳሴ እግዚእ “እምድንግል ተወሊዶ ከመ ፈቃደከ ይፈጽም” ብሎ ድንግልን ያነሣታልና፡፡
አባ ሕርያቆስ ተሹሞ ሳለ ብዙ ድርሳን እንደደረሰና ብዙ ተግሳጽ እንደጻፈ የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ይገልጻል፡፡

---------ከቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊና ከቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ ጋር

ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ መደበይ ታብር በሚባል ቦታ ይኖር ነበር፡፡ እመቤታችን ኤፍሬምን ከሶርያ አባ ሕርያቆስን ከብህንሳ በደመና ጠቅሳ ያሬድ ካለበት ቦታ አመጣቻቸውና “አንተ(ኤፍሬም) ውዳሴዬን አንተ(ሕርያቆስ) ቅዳሴዬን ነግራችሁት እርሱ(ያሬድ) በዜማ ያድርስ” ብላቸው፣ እነርሱም ለቅዱስ ያሬድ ነግረውት በዜማ አድርሶታል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ከዚኽ ጋር አያይዞ የቀሩትን 13ቱን ቅዳሴያት ኹሉ በዜማ ደርሷል፡፡

--------እመቤታችን የምትወደው ምስጋና

አንድ ባሕታዊ እመቤታችንን “ከምስጋናሽ ኹሉ ማንን ትወጃለሽ?” ብሎ ቢጠይቃት “ልጄ ዳዊትን፣ አቡነ ዘበሰማያትን ቢደግሙለት እንዲወድ እኔም ውዳሴዬን ቅዳሴዬን ቢደግሙልኝ እወዳለሁ” ብላዋለች፡፡

----------.ብህንሳ የት ናት?

ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ስለ ብህንሳ የሚከተለውን ብሏል፡-
“ብህንሳ ቅድመ ትሰመይ አርጋድያ ወድኅረ መኑፍ ይላል፡፡ ብዙ ጊዜ ስመ ተፋልሶ አግኝቷታል፡፡ በፊት አርጋድያ ኋላም መኑፍ ተብላለች፤ ዛሬም ብህንሳ ትባላለች፤ ሴትና ወንድ ያልተለየባት ገዳም ናት እንደ ዘጌ እንደ ቆራጣ እንደ ቀንጠፋሜ፤”

ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ የባሕር ማዶ ድርሰት መኾኑን በሚጠቁም መልኩ ቅዱስ ያሬድ ከባሕር ወዲኽ እንዳመጣልንና ከተከዜ ወዲኽ ደግሞ ሳሙኤል ትውልደ ጌዴዎን ዘገበዘ አክሱም እንዳመጣው ይገልጻል፡፡ ስለዚህ ቢንያስ እንደ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ኢትዮጵያ ውስጥ አይደለችም።

Kyriakos of bhainsa ስለተባለ ሰው Wikipedia ቢገልጽም ዝርዝር መረጃን አላገኘሁም። Bhainsa የምትባል ከተማ ግን በሕንድ እንምደትገኝ ይገልጻል።

በዚኽ ዙሪያ ጥናት ያደረጋችኹ ወይም ተጨማሪ ያነበባችሁና የተማራችሁ እስኪ ሐሳባችሁን ወዲኽ በሉ፤ ፍላጎቱ፣ አቅሙና ጽናቱ ያላችሁም በጥልቅ መርምሩና ግለጡልን፡፡

የአባታችን የአባ ሕርያቆስ ምልጃ አይለየን፤ እመቤታችን ፍቅሯን በረከቷንና የምስጋናዋን ምሥጢር በልቡናችን ታሳድርልን ዘንድ በረድዔቱ ይባርከን፡፡

ጥቅምት 2፣ 2007 ዓ.ም.
7.4K viewsYadesa Damena, 05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-03 20:51:50
ፎቶ ከማኅበራዊ ሚዲያ
4.1K viewsYadesa Damena, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-03 20:51:35 ከሰማዕታቱ በረከት ይክፈለን

መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ከሰኔ 22 ቀን 2012ዓ.ም. ሌሊት ጀምሮ በተከታታይ ለሁለትና ሦስት ቀናት በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በአረመኔዎች ሰማዕትነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች መታሰቢያ መሆኑን ሀገረ ስብከቱ አስታውቆ እንደነበር ይታወቃል።
ሰማዕታቱን ለመዘከርም ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ቦታው አምርተዋል። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ በክርስቲያኖዊ ጥብዓት ሰማዕትነትን ሲቀበሉ በተግባራቸው ብትኮራም አሁንም መከራ ላይ የማጥናትና ለሟች ወገኖች አለኝታ በመሆን ከሰማዕታቱ በረከት እንዲካፈሉ ልጆቿን ተግታ ማስተማርም ይኖርባታል። የሟች ወገኖቻችንን ቀሪ ዘመዶች መርሳት ከገዳዮች ጋር መተባበር መሆኑን ክርስቲያኖች መረዳት ይኖርብናል።
መንግሥትን ፍትሕ ተዳፍና እንዳትቀር የምንወተውተውን ያህል ክርስቲያኖችም በመከራ ውስጥ ያሉትን ወገኖቻችንን በማጽናትና የተጎዱትን በመደገፍ አይዟችሁ ባይ ወገን እንዳላቸው በተግባር መግለጥ ይኖርብናል። በክርስቲያኖች የደረሰውን መከራ ሳናዛንፍ ለዓለሙ ሁሉ ማሳወቅ ተገቢ የመሆኑን ያህል ምግብ፣ ልብስ፣ መጠለያና ቋሚ መተዳደሪያ በማጣት ክርስቲያን በመሆናቸው ብቻ በደረሰባቸው መሪር ኀዘን ተስፋ እንዳይቆርጡ መደገፍም የክርስቲያኖች ተግባር መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል። መከራውን ለመቋቋም መተባበርና አንድ አሳብ መሆንም ዘመኑ የሚጠይቀን ግዴታ ነው። ዘመኑን መሻገር የምንችልበትን ተግባር መፈጸም ብቻ ሳይሆን ዘመኑን ዋጅተን የቤተ ክርስቲያንን ብርሃንነት መግለጥም ክርስቲያናዊ ኃላፊነታችን ነው።




ከ @mkpublicrelation የተወሰደ
4.1K viewsYadesa Damena, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-28 12:16:01 "ሰይጣን የማይነካው ዕቃ "

በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ።
የበዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ።
ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ።
"እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ
በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው "
ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው።
ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው።
" የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው።
ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት።
ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት።
ይህን ግዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት።
በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም። አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ።
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ»
«በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!

ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
4.9K viewsYadesa Damena, 09:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ