Get Mystery Box with random crypto!

✞ገድለ ቅዱሳን✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ kegdlat — ✞ገድለ ቅዱሳን✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ kegdlat — ✞ገድለ ቅዱሳን✞
የሰርጥ አድራሻ: @kegdlat
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.13K
የሰርጥ መግለጫ

✝✞ከኢ/ኦ/ተዋህዶ ቤ/ክ ላይ የተገኙ የየዕለቱ የቅዱሳን አባቶቻችን እና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድል ይነገርበታል✝

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-02-13 19:27:08 ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት ስድስት(፮)
https://t.me/SinkisarZekidusan2
1.6K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 19:25:44 † † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን † †

††† እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

+*" ቅድስት ማርያም "*+

=>ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: (ሉቃ. 7:36-50)

+ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ:-
1.ትርጉዋሜ ወንጌልን
2.ተአምረ ኢየሱስን
3.ስንክሳርን እና
4.መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

+እንት ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማለት ነው) ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን (በዘመነ ስብከቱ) የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

+በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት (መስማት) እጅግ ያሳዝናል::

+በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን (እህቶቻችንም) ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

+ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

+ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት (መስታውት ማለት ነው) ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና (የሚያስተውለው ቢገኝ) ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

+እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

+መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

+የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም:: ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::
1.ከውስጧ እንባዋን:
2.ከአካሏ ጸጉሯን:
3.ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

+ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

+*" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "*+

=>የዓለም ሁሉ መምህር:
¤ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤38 ሕግጋትን የደነገገ:
¤ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

+አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት 5 ሲሆን የካቲት 6 ሥጋው የተገኘበት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

=>የካቲት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
2.የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ (ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት)
3.ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ (ሰማዕታት)
4.ቅድስት አትናስያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

=>+"+ . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: +"+ (ሉቃ. 7:46)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
1.6K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 08:02:47 + +  +እግዚአብሔር አምላክ ለሀገራችን እና ላለንበት ሀገር ሰላምን ይስጥልን አሜን++

መጽሐፈ ስንክሳር፣
ከዲ/ን ዮርዳኖስ ማስታወሻ

+++መልካም ዕለተ አርብ መልካም ቀን።
+++
505 views05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 08:02:11
510 views05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 08:01:43 ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት ሦስት(፫)
https://t.me/SinkisarZekidusan2
479 views05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 08:01:11 ✞ ✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞ ✞

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ የካቲት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+" ቅዱስ ማሪ ኤፍሬም ሶርያዊ "+

+እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ቅዱስ ኤፍሬም
የተወለደው ንጽቢን በምትባል የሶርያ ግዛት ውስጥ
በ298 / 306
ዓ/ም ነው:: ወላጆቹ በክርስቶስ የማያምኑ አላውያን
ነበሩ:: (ምንም አንዳንድ ምንጮች ክርስቲያኖች ነበሩ
ቢሉም)

+ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ንጽቢን ዽዽስናን የተሾመ
ቅዱስ ያዕቆብ የሚባል ታላቅ ሰው ነበር:: የሰማዕትነት:
የሐዋርያነት: የጻድቅነትና የሊቅነት ግብር ያለው አባት
ነው:: ታዲያ ቅዱስ ኤፍሬም ይሔ አባት ሁሌ ሲያስተምር
ይሰማው
ነበርና በስብከቱ ተማርኮ ደቀ መዝሙሩ ለመሆን በቃ::

+ቅዱስ ኤፍሬም በቅዱስ ያዕቆብ እጅ ከተጠመቀ በሁዋላ
ሙሉ የጣትነት ጊዜውን ያሳለፈው በትምሕርት ነው::
የሚገርመው
መምሕሩ ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን እመቤታችን ድንግል
ማርያምን በፍጹም ልቡ የሚወድና ጠርቷት የማይጠግብ
አባት ነውና ለልጁ
ለቅዱስ ኤፍሬም ይሕንኑ አጥብቆ አስተምሮታል::

+ቅዱስ ኤፍሬም ክርስትናን ሲመረምር የእመቤታችን
ፍቅር ይበዛለት ጀመር:: ምክንያቱም እመ ብርሃንን
ሳይወዱ ክርስትና
የለምና:: እንደ እርሱ የሚወዳት የለም እስኪባል ድረስ
ያገለግላት: ይገዛላትም ገባ::

+እንዲህ እንደ ዛሬ የድንግል ማርያም ምስጋና በአንደበት
እንጂ በመጽሐፍ አይገኝም ነበር:: እርሱ ግን ከወንጌለ
ሉቃስ
በስድስተኛው ወርን (ይዌድስዋን) እና ጸሎተ ማርያምን
(ታዐብዮን) አውጥቶ በየዕለቱ በዕድሜዋ ልክ 64 64
ጊዜ
ያመሰግናት ነበር::

+በእንዲህ ያለ ግብር እያለ አርዮስ በመካዱ እርሱን
ለማውገዝና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ለማጽናት በ317 /
325
ዓ/ም 318ቱ ሊቃውንት በኒቅያ ሲሰበሰቡ አንዱ መምሕረ
ኤፍሬም ቅዱስ ያዕቆብ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ
ኤፍሬም
ከሊቃውንቱ ትምሕርትና በረከትን አግኝቷል::

+ከጉባዔ መልስ መንገድ ላይ በራዕይ የብርሃን ምሰሶ
አይቶ "ጌታ ሆይ! ምንድን ነው?" ብሎ ቢጠይቅ "ይህማ
ታላቁ ቅዱስ
ባስልዮስ ነው" አለው:: እርሱም መምሕሩን ቅዱስ
ያዕቆብን ተሰናብቶ ወደ ቅዱስ ባስልዮስ (ቂሣርያ) ወረደ::
ተገናኝተውም በአንድ ሌሊት ቁዋንቁዋ ተገልጦላቸው
ሲጨዋወቱ አድረዋል::

+በቦታው ብዙ ተአምራት ተደርጉዋል:: ቅዱስ ኤፍሬም
ከታላቁ ባስልዮስ ከተማረ በሁዋላ ሃገረ ስብከት
ተሰጥቶት ያስተምር
ጀመር:: ሁል ጊዜ ታዲያ ጸሎቱ ይሔው ነበር:: "እመቤቴ
ሆይ! ምስጋናሽ እንደ ሰማይ ከዋክብት: እንደ ባሕር አሽዋ
በዝቶልኝ: እንደ እንጀራ ተመግቤው: እንደ ውሃ ጠጥቼው:
እንደ ልብስም ተጐናጽፌው" እያለ ይመኝ ነበር::

+አፍጣኒተ ረድኤት: ፈጻሚተ ፈቃድ እመ ብርሃንም በገሃድ
ተገልጻ የልቡን ፈቃድ ፈጸመችለት:: ዛሬ ጸጋ በረከት
የምናገኝበትን ውዳሴ ማርያምን ደረሰላት:: ሲደርስላትም
እርሷ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላ
ወርዳ:
በፊቱም ተቀምጣ ሲሆን እርሱ ደግሞ ባጭር ታጥቆ:
በፊቷ ቆሞ: በመንፈስ ቅዱስም ተቃኝቶ ነው::

+ውዳሴዋን በ7 ቀናት ከደረሰላት በሁዋላ በብርሃን
መስቀል ባርካው: ሊቀ ሊቃውንትም እንዲሆን ምስጢር
ገልጣለት
ዐረገች:: ከዚህ በኋላ በምስጢር ባሕር ውስጥ ዋኝቶ 14
ሺህ ድርሰቶችንም ደርሷል:: ዛሬ ሶርያ ውስጥ
የምንሰማውን
ዜማም የደረሰው ይህ ቅዱስ ነው::

+እንዲያውም አንድ ቀን የምሥጢር ማዕበል ቢያማታው
"አሃዝ እግዚኦ መዋግደ ጸጋከ" ብሎ ጸልዩዋል:: (የጸጋህን
ማዕበል
ያዝልኝ) እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
በመጨረሻ ሕይወቱ ተክሪት በምትባል ሃገር ኤዺስ ቆዾስ
ሆኖ ተሹሟል::

+በጣፋጭ ስብከቱ ብዙዎችን ካለማመን መልሷል:
የምዕመናንንም ሕይወት አጣፍጧል:: ለመናፍቃንና
ለአርዮሳውያን ግን
የማይጋፉት ግድግዳ ሆኖባቸው ኑሯል:: በዘመኑም ብዙ
ተጋድሎ አፍርቷል: ተአምራትንም ሠርቷል:: በተወለደ
በ67 ዓመቱ
በ365 / 373 ዓ/ም ዐርፎ ተቀብሯል::

+ቅዱሱ ለሶርያ ብቻ ሳይሆን እመቤታችንን ለምንወድ
የዓለም ክርስቲያኖች ሁሉ ሞገሳችን ሆኗል:: ስለዚህም
እንዲህ እያልን
እንጠራዋለን:-

1.ቅዱስ ኤፍሬም
2.ማሪ ኤፍሬም
3.አፈ በረከት ኤፍሬም
4.ሊቀ ሊቃውንት
ኤፍሬም
5.ጥዑመ ልሳን ኤፍሬም
6.አበ ምዕመናን
ኤፍሬም
7.ርቱዐ ሃይማኖት ኤፍሬም . . . አባታችን አንተ ነህ::

❖የካቲት ፫ ቀን ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ዓመታዊ የፍልሠት በዓሉ ነው፡፡

✞ጽንዕት በድንግልና: ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን
ለቅዱስ ኤፍሬም የሰጠሽውን ጸጋውን: ክብሩን:
አእምሮውን: ለብዎውን
በልቡናችን ሳይብን: አሳድሪብን . . . አሜን::

+" አባ ያዕቆብ ገዳማዊ "+

+ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ዳዊት "ለስሒት መኑ ይሌብዋ-
ስሕተትን ማን ያስተውላታል" (መዝ) ሲል የተናገረው
ይፈጸም ዘንድ ይህ
ታላቅ ቅዱስ ሰው በኃጢአት ብዙ ተፈተነ:: ወደ በርሃ
ወጥቶ: በምናኔ ጸንቶ: በጾምና በጸሎት ተግቶ ዘመናትን
ስላሳለፈ
ሰይጣንን አሳፈረው::

+ግን ደግሞ ክፉ ጠላት ባልጠረጠረው መንገድ መጥቶ
መከራ ውስጥ ከተተው:: የአገረ ገዢው ልጅ ታማ
"ፈውሳት" አሉት:
ፈወሳት:: ወደ ቤቷ ስትመለስ ግን አመማት:: "ከአንተ ጋር
ትቆይ" ብለው ትተዋት ቢሔዱ ከመለማመድ የተነሳ
በዝሙት
ወደቀ::

+እንዳይገለጥበት ስለ ፈራም ገደላት:: በሆነው ነገር
ተስፋ ቆርጦ ወደ ዓለም ሲመለስ: ቸር ፈጣሪ የሚናዝዝ
አባትን ልኮ
ንስሃ ሰጠው:: ጉድጓድ ምሶ: ድንጋይ ተንተርሶ ለ30
ዓመታት አለቀሰ:: እግዚአብሔርም ምሮት: የቀደመ
ጸጋውን
ቢመልስለት: ዝናምን አዝንሞ ሕዝቡን ከእልቂት ታድጓል::
በዚህች ዕለት ዐርፎም ለርስቱ በቅቷል::

+" ታላቁ አባ ዕብሎይ "+

+ይህ ቅዱስ የአቡነ አቢብ ደቀ መዝሙር ሲሆን በዚህ
ስም ከሚጠሩ ቅዱሳንም ቀዳሚው ነው:: ብዙ መጻሕፍት
'ርዕሰ
ገዳማውያን' ይሉታል:: የቅዱሱ ተጋድሎ እጅግ ሰፊ ነው::

✞የካቲት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት-በዓለ ፍልሠቱ)
2.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ (ሕይወቱ መላዕክትን
የመሰለ ግብፃዊ አባት)
3.አባ ያዕቆብ መስተጋድል

++"+ ለምኑ ይሰጣችሁማል:: ፈልጉ ታገኙማላችሁ::
መዝጊያ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል:: የሚለምነው ሁሉ
ይቀበላልና::
የሚፈልገውም ያገኛል:: መዝጊያንም ለሚያንኳኳ
ይከፈትለታል:: +"+ (ማቴ. 7:7)

++"+ የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::አንደበቱም
ፍርድን ይናገራል::የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም
አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 37:30)

✞ ✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞ ✞
448 views05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 08:12:34 + +  +እግዚአብሔር አምላክ ለሀገራችን እና ላለንበት ሀገር ሰላምን ይስጥልን አሜን++

መጽሐፈ ስንክሳር፣
ከዲ/ን ዮርዳኖስ ማስታወሻ

+++መልካም ዕለተ ሐሙስ መልካም ቀን።
+++
1.6K views05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 08:11:51
1.5K views05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 08:11:15 ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት ሁለት(፪)
https://t.me/SinkisarZekidusan2
1.3K views05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 08:10:12 የካቲት ፪ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ አባ ጳውሊ ገዳማዊ (የባሕታውያን ሁሉ አባት)
፪.ቅዱስ አባ ለንጊኖስ ሊቀ ምኔት (ደብረ ዝጋግ)
፫.ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
††† ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
፪.ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
፫.ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ (የሃይማኖት
ጠበቃ)
፬.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ
፭.ቅዱስ አቤል ጻድቅ
፮.አባ ሕርያቆስ ዘሐገረ ብሕንሳ

††† "የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ። ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ። በድንጋይ ተወግረው ሞቱ። ተፈተኑ፤ በመጋዝ ተሰነጠቁ፤ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ። ሁሉን እያጡ፣ መከራን እየተቀበሉ፣ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ። ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ በዋሻና በምድር ጉድጓድ ተቅበዘበዙ።" †††
(ዕብ ፲፩፥፴፭-፴፰)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
1.1K viewsedited  05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ