Get Mystery Box with random crypto!

❝እነሆም የስራ ዜና!❞ * *** #ለሸፍቴ_ቅዱስ_ሩፋኤል_ህንጻ_ማሰሪያ_201000_ብር_ገቢሆነ | ከ



❝እነሆም የስራ ዜና!❞
* ***

#ለሸፍቴ_ቅዱስ_ሩፋኤል_ህንጻ_ማሰሪያ_201000_ብር_ገቢሆነ!

በደቡብ ክልል በጎፋ ዞን በኦይዳ ወረዳ በሸፍቴ ከተማ ለምትገኘው የቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ህንጻ ማሰሪያ ከዚህ ቀደም ህንጻው ተጀምሮ ከ10 ዓመታት በላይ ቆሞ ቀርቶ የነበረውን ለማሰራት እንቅስቃሴ ጀምሬ የተባረከው ወንድሜ ከአሜሪካን ሃገር ከኪሱ እና ደጋጎችን አስተባብሮ ከዚህ ቀደም 208,000 ብር ሌላም ጊዜ ከ100,000 ብር በላይ በድምሩ ከ310,000 ብር በላይ ልኮ ቆሞ ቀርቶ የነበረው የሩፋኤል ህንጻ መጀመሩ እና ትልቅ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አብስሬ ነበር። እነሆም ይሄው ወንድሜ ከሃገረ አሜሪካ 201,000 (ሁለት መቶ አንድ ሺህ) ብር ልኮልናል። እስከ አሁን ድረስ ለሸፍቴ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ህንጻ ማሰሪያ የሚሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ ስሙን እንድገልጽ በማይፈልገው ወንድሜ ከሃገረ አሜሪካ ሰጪነት ከ501,000 ብር በላይ ገንዘብ ገቢ ሆኗል።

እናንት የሸፍቴ ከተማ ነዋሪዎች፥ ይህ መቅደስ ሲያልቅ ለኦርቶዶክስ አማኙ ብቻ ሳይሆን ለሁላችሁ የከተማችሁ ድምቀት ነውና ህንጻውን ተባብራችሁ ከዳር እንድታደርሱት አደራ እላለሁ። ገንዘቡን ሳትሰስት የምትቸረን ወንድሜ ገንዘቡ በትክክል ለታለመለት አላማ እየዋለ ነውና ደስ ይበልህ። የአምላክን ቤት ለመስራት ገንዘብህን ለመስጠት እጅህ አልሰሰተምና ስስት የሌለው የአምላክ በረከት ቸርነት በቤትህ ይሁን እላለሁ። አምላክ ለፍጻሜው በሰላም ያድርሰን። እንድንጨርሰውም አቅሙን ይስጠን!

https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet