Get Mystery Box with random crypto!

ፆመ ነነዌ ነብዩ ዮናስ ሦስት ቀንና ሌሊት በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሰነበተ ፤ ዮናስም በዓሣው ሆድ | 💎ስለ ማርያም አማላጅነት እንመሰክራለን✍

ፆመ ነነዌ
ነብዩ ዮናስ ሦስት ቀንና ሌሊት በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሰነበተ
፤ ዮናስም በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፥ እንዲህም አለ።
፤ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ፥ ቃሌንም አዳመጥህ።
፤ ወደ ጥልቁ ወደ ባሕሩ ውስጥ ጣልኸኝ፥ ፈሳሾችም በዙሪያዬ ነበሩ፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፉ።
፤ እኔም። ከዓይንህ ፊት ተጣልሁ፤ ነገር ግን ወደ ቅዱስ መቅደስህ ደግሞ እመለከታለሁ አልሁ።
፤ ውኆችም እስከ ነፍሴ ድረስ ከበቡኝ፤ ጥልቁ ባሕር በዙሪያዬ ነበረ፤ የባሕሩ ሣር በራሴ ተጠምጥሞ ነበር።
፤ ወደ ተራሮች መሠረት ወረድሁ፤ በምድርና በመወርወሪያዎችዋ ለዘላለም ተዘጋሁ፤ አንተ ግን፥ አቤቱ አምላኬ፥ ሕይወቴን ከጕድጓዱ አወጣህ።
፤ ነፍሴ በዛለችብኝ ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብሁት፤ ጸሎቴም ወደ አንተ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ገባች።
፤ ከንቱነትንና ሐሰትን የሚጠብቁ ምሕረታቸውን ትተዋል።
፤ እኔ ግን በምስጋና ቃል እሠዋልሃለሁ፤ የተሳልሁትንም እከፍላለሁ። ደኅንነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።
፤ እግዚአብሔርም ዓሣውን አዘዘው፥ እርሱም ዮናስን በየብስ ላይ ተፋው።
(ትንቢተ ዮናስ ምዕ. 2ቁ2-11)
በሦስተኛ ቀኑ ከነነዌ የባህር ዳርቻ ሲደርስ  ተፋው። እግዚአብሔርን አመሠገነ። ወደ ነነዌ ከተማ ገባ። ያለማይክ ሕዝቡን ሰበከ። ከህጻን እስከ አዋቂ፣ ከእንስሳ እስከ ሰው፣ ከሎሌ እስከ ንጉሥ ድረስ  አዳመጡት። በክፋታቸው ተጸጸቱ። ጾሙ፣ ራሳቸውን ስለ እግዚአብሔር አዋረዱ። እግዚአብሔርም ማራቸው። /

ነብዩ ዮናስ ሆይ ባንተ ስለሆነ ዳግም የኛ ተስፋ
አንዴ ተነስና ቀንደ መለከቱን በምድር ላይ ንፋ
የፍርድ ፅዋው ሞልቶ....
ዳግማዊ ነነዌ ኢትዮጵያ እንዳትጠፋ