2022-06-25 21:30:44
#በእርግጥም_አምላክ_ተሸነፈ።
#በጥንቃቄ_ይነበብ።
የሰውን ልጆች ሁሉ በጥልቅ ፍቅር የሚወድ ጌታ የሚወደው አልዓዛር የሚባል ሰው መታመሙን በመልእክተኛ በመላክ የአልዓዛር እህቶች ሁሉን ለሚያውቀው ጌታ ነገሩት። ያኔ እርሱ በኢየሩሳለም ጴርያ በምትባል አካባቢ ነበር። እናም አይሁድ ኢየሱስን ለመግደል በተደጋጋሚ ሙከራ ባደረጉበት በይሁዳ ግዛት ወደምትገኘው ቢታንያ #በተነገረው ጊዜ ሳይሆን አልዓዛር ሞቶ በተቀበረ #በ4ኛው ቀን ደረሰ ።
ቢታኒያ ሲደርስ ጌታን በማስተናገድ የምትተጋው ማርታ ቀድማ ልትቀበለው ወጣች ። ስታገኘውም #አንተ_እዚህ_የነበርክ_ቢሆንኮ_ወንድሜ_አይሞትም_ነበር። አለችው
የሚገርመው ግን ለአብ እና ለወልድ ክብር ሲባል ነፍሱን ከስጋው የለየውን ጌታ ነበር እንዲህ ያለችው። #ለዚያውም_ህመሙ_እንኳን_ለሞት_የሚያበቃ_አልነበረም።
“ኢየሱስም ሰምቶ፦ ይህ ህመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ #ይከብር #ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው #እንጂ #ለሞት #አይደለም አለ።”
ዮሐ 11፥4
ታዲያ ይህን ሀያል አምላክ በዚህ ብትገኝ ጉድ ባልሆንን ነበር አለችው። #በእርግጥ_ጌታ_በዚያ_ነበርኮ_ግን በጴርያ ሳለ አልዓዛር መሞቱን ለደቀመዛሙርቱ ነግሯቸዋልኮ። ካለ እርሱ እውቅና የሚሆን አንዳች ነገር የለምና #ሁሉ_ሲሆን እርሱ በእርግጥ በዚያ አለ። ታዲያ ይህ ቸር ጌታ የሚፈውስ እንጂ #ህይወት_የሚሰጥ መሆኑን ብትዘነጋውም #ሰማይና_ምድርን በእጆቹ መዳፍ የሚይዘውን በቦታ ብትገድበውም እርሱ ግን #ወንድምሽ_ይነሳል አላት ። እምነቷ ቢፈተን በትንሳኤ ቀን ይነሳል አለችው።
“ኢየሱስም፦ #ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤”
ዮሐ11፥25 በማለት መድሃኔአለም እርሱ #ህይወት መሆኑን #ህይወት_የሚገኘውም_በክርስቶስ_በማመን መሆኑን ይህን ታምን እንደሆን ማርታን በመጠየቅ ታላቅ ትምህርት አስተማረን።
ከዚያም ሄዳ እህቷ ማርያምን ወደእርሱ ጠራቻት። #ማርያምም ፈትለክ ብላ ሊያፅናኑአት የመጡትን ጥላ ወጣች።መቃብር ሄዳ ልታለቅስ መስሏቸው ቢከተሉአትም #አሁን_ግን_የምታለቅሰው_በንጉስ_እግሮች_ስር_ነው።
በፍጥነት ማርታን ካገኘበት ስፍራ እንኳን ሳይንቀሳቀስ #እየሮጠች_ሄዳ_ከአዛኙ_እግር_ስር_ተደፍታ_ማልቀሷን ቀጠለች።
#ይሄን_ጊዜ_አምላክ_ተሸነፈ።
ምንም የማያሸንፈው አምላክ #ሃዘን_ባደቀቃት_እግሮቹ_ስር_ተደፍታ_በምታነባ_ነፍስ_ፍቅር_ተሸነፈ።
“ኢየሱስም እርስዋ ስታለቅስ ከእርስዋም ጋር የመጡት አይሁድ ሲያለቅሱ አይቶ #በመንፈሱ አዘነ በራሱም #ታወከ፤”
ዮሐ 11፥33
#ይሄ_እንዴት_የሚደንቅ_ነው??
ከተወሰኑ ደደቂቃዎች በሁዋላ #ከሞት_ሊያስነሳው_እንደሆነ_እያወቀ #የሚወዳቸውን_እንባ_አይቶ_አይጨክንምና_መንፈሱ_እርብሽ_ብሎ_ታወከ። ጌታችን ከፈጠራቸው ጋር #አዘነ።
በዚህ ጊዜ አንዳንዶቹ #የሚያለቅሰው ምንም ማድረግ ሳይችል ቀርቶ መስሏቸው ማንሾካሾክ ጀመሩ። ባለፈው #የአይነስውሩን አይኖች ሲከፍት አልነበር ዛሬ አልዓዛር እንዳይሞት ማድረግ ከበደው መሰል ይሉ ጀመር
ግና አልዓዛርን ከሞት ማስነሳት ከእንቅልፉ የመቀስቀስ ያህል የሆነለት ጌታ ነው እርሱ። ( #ዮሐንስ #11: 11&13)
ሲጀመርም ለአምላክ ክብር ነፍሱን ከስጋው የለየ ጌታ #ራሱ_አይደል??
ሊያስነሳውስ መጥቶ እንዴት አብሯቸው #ያዝናል??
#ሩህሩህ ነዋ የኛ ጌታ #በፊቱ_ስናነባ አብሮን የሚያዝን ማሪያም በእግሮቹ ስር ተደፍታ
ያነባችው እንባ መንፈሱን እርብሽ አድርጎት #ፍቅር_የሆነ_አምላክ_በፍቅር_ቢሸነፍ እንባው #ፍስስ አለ።
“ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።”
ዮሐ 11፥35
ይቀጥላል ... ለቀጣዩ join
@untothelamb
@untothelamb
@untothelamb
304 viewsⓈ ⓘ, 18:30