Get Mystery Box with random crypto!

#እኔ_ነኝ_አልዓዛር ... አምላክ ተሸነፈ #Part_2 “ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።” — ዮሐ | የአዲስ ኪዳን ካህናት

#እኔ_ነኝ_አልዓዛር ... አምላክ ተሸነፈ #Part_2

“ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።”
— ዮሐንስ 11፥35

ከደቂቃዎች በኋላ ከምት ሊያስነሳው ሳለ ማልቀስ ምን አስፈለገው ?? እዩልኝ የጌታዬን ፍቅር : ማርያም እግሮቹ ስር ተደፍታ ስታነባ የጌታችን አንጀት ተላወሰ: አብሯቸው አለቀሰ።
#በምንም_አይነት_በደል : #ድካም : #ሀዘን : #ብቸኝነት : #ተስፋ_መቁረጥ እግሮቹ ስር ድፍት ብለው ለሚያነቡ በሀዘን ለደቀቁ ነብሶች : ለተሰበሩ ልቦች ጸሎትን ከመመለስ #ያለፈ ነውና ጌታችን : ሀዘንችንን የሚካፈል ርህራሄውም የማያልቅ ነውና #መፀለያችሁን : #እግሮቹ_ስር_መደፋታችሁን መቼም እንዳታቆሙ !!

#ይገባዋል : #ይረዳናል #ይራራልናል : #ህመማችንን ይካፈላል ።

“እርሱ ራሱ ተፈትኖ መከራን ስለ ተቀበለ የሚፈተኑትን ሊረዳቸው ይችላልና።”
— ዕብራውያን 2፥18

በተጠቀሰው ክፍል ለክርስቶስ እንባውን ማፍሰስ ከታላቅ ፍቅሩ በስተቀር ምክንያት : ከርህራሄው በስተቀር ሰበብ የለንም።

ደርሶም በመቃብሩ የተጫነበትን ድንጋይ አንሱ ቢላቸው : የገዛ እህቱ #ይሸታል አለች( አልዓዛርስ 4 ቀኑ ለዘመናት በሃጢያት የሞትን እኛ እንደምን እንብስ??)
ከዚያም በእምነት የእግዚአብሔርን ክብር እንደምታይ ነገራት።

#ይሄ_ሁሉ_አልበቃ ብሎት ቸሩ ጌታ #የሞተውን(እኛ ሬሳ የምንለውን ) እርሱ አልዓዛር ሆይ ብሎ #በስሙ ጠራው ።እኛማ የምንወደው ሰው እንኳ ለሞት ከሆነ እንፈራው የለ : የክርስቶስ ፍቅር ግን ከመቃብርም ያለፈ ነው።

#በሃያል_ድምፁ_ሞት_ተንበረከከ!! እኛም የሚያፅናናንን የትንሳኤ ተስፋ በዚህ ቃል ብርሃን ተመለከትን። ክብር ለስሙ ይሁን።

#ከነመግነዙ አልዓዛር ከመቃብር ወጣ። በአይሁድ ዘንድ ተሰምቶ የማይታወቅ ነገር ሆነ ።

ጌታም ፍቱትና ይሂድ ብሎ በነፃነት እንዲኖር ነፃ አወጣው።
#እኔ_ነኝ_አልዓዛር ... See the aamazing operation of #GRACE here

ልክ እንደ አልዓዛር #እኔም_ሙት ነበርኩኝ። በሃጢአት ታምሜ በሞት ተቀጣሁኝ ። የኔ ጌታ ባለበት መች ቆየ : እኔ ወዳለሁበት ወረደ : ባለበት ሆኖ አይደለም ያዳነኝ : ሰው ሆኖ መጥቶ ነው ። ለአልዓዛር እንባውን በሀጥያት ለሞትኩት ለእኔ ግን #ደሙን አፈሰሰልኝ ። የበደልና የሀጥያትን #ድንጋይ ከላዬ አንከባለለ። #በስሜ ቢጠራኝ ወደ እርሱ መጣሁ። የሀጥያትና የሞት ሰንሰለቴን በጣጥሶ #ፈቶ ለቀቀኝ። ክብር ምስጋና ይግባው !!

እባካችሁ ወደሚወዳችሁ ክርስቶስ ኑ!! እመኑ በእርሱ ያድናችኋል ።

“እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።”
— ራእይ 3፥20

@untothelamb
@untothelamb
@untothelamb