2021-05-22 16:03:56
good news!
ተጨማሪ ፦
በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ልምድ እና አቅም ያላቸው የውጭ ኩባንያዎች እንዲሳተፉ ለማድረግ ለረጅም ጊዜ ሲሰራ ነበር።
በዚህ መሰረት ሜይ 21/2020 በኢትዮጵያ ኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ለቀረበው ጥሪ 12 ኩባንያዎች በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይተው ነበር።
ከነዚህ መካከል 9 ድርጅቶች የጨረታ ሰነዱን ገዝተዋል።
በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል የተቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ ባደረገው ማጣራት ቴክኒካል እና ፋይናሻል ፕሮፖዛል ያቀረቡ ሁለት ኩባንያዎች ፦
• Global partnership for Ethiopia (Vodafone, Vodacom, Safaricom, Sumitomo Corporation, and the CDC Group የተባሉ ዓለም አቅፍ የቴሌኮም ኩባንያዎች በጥምረት ያቋቋሙት ኩባንያ) እና
• MTN International (Mauritius) Limited የተሰኙ ኩባንያዎች ጨረታውን መስፈርቶች አሟልተው ተገኝተዋል።
ለተጠቀሱት ድርጅቶች ለሁለቱም /ለአንዱ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ፍቃድ እንዲሰጥ አልያም የጨረታቅ ውጤት እንዲሰረዝ እንዲወሰን ለሚኒስትሮች ም/ቤት ቀርቦ ነበር።
ምክር ቤቱ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው ድርጅት ፦
- የኦፕሬሽን ፈቃድ ለማግኘት ያቀረበው ዋጋ 850 ሚሊዮን ዶላር (ከ2ኛ ድርጅት ዋጋ በ250 ሚሊዮን ዶላይ ብልጫ አለው) ፥
- ለ1.5 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ስለሚፈጥር፣
- ከ8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት በአገር ውስጥ የሚያከናውን ስለሆነ እና ካለው የስራ ልምድ አንፃር ለኢትዮጵያ ጥራት ያለድ የቴሌኮም አገልግሎት ለማቅረብ አቅም ያለው መሆኑን ከግምት በማስገባት (Global partnership for Ethiopia) የኦፕሬሽን ፍቃድ እንዲሰጠው ተወስኗል።
1.9K views13:03