የተሳሳተ መረጃ ስለማረም ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በቲክቶክ በተለቀቀ የተሳሳተ መረጃ የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝግባችሁ እየተጠባበቃችሁ ያላችሁ ብቁ መሆን አለመሆናችሁን ባምቢስ በሚገኘው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ 5ኛ ፎቅ መታችሁ እንድታዩ በሚል የተለቀቀው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን እየገለፅን ተመዝግባችሁ እየተጠባበቃችሁ የምትገኙ ላተፈለገ እንግልት እንዳትዳረጉ የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ይገልፃል፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ እና ኮርፖሬሽኑ ነዋሪውን በተለይም ተመዝግቦ የሚጠባበቀውን የቤት ባለቤት ለማድረግ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ከምንጊዜውም በተሻለ መልኩ እየሰሩ እንደሚገኝ እየገለፅን ተመዝጋቢዎችም ሆነ ሌሎች ነዋሪዎች የተቋሙ ባልሆኑ ማህበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ ግለሰቦች በሚያናፍሱት ወሬ እንዳትታለሉ እያስገነዘብን ትክክለኛውን የቤት መረጃ ለማግኘት ከታች ያሉትን የማህበራዊ ሚዲያ ሊንኮች ብቻ እንድትጠቀሙ እናሳስባለን፡፡ የአ/አ/ል/ አስተዳደር ቢሮ 16.7K views08:09