በዛሬው እለት 435 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለመምህራን በዕጣ እንዲተላለፉ አድርገናል። ከዚህ በፊት ለመምህራን ተላልፈው ከነበሩ 5 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ውል ሳይፈጸምባቸው የቆዩ 435 ቤቶችን በማጣራት ከለየን በኋላ ዛሬ በዕጣ ለቤት እድለኞቹ አስተላልፈናል። ያለንን ውስን ሃብት በግልፀኝነትና በፍትሃዊነት በተገቢ ሁኔታ ለህዝባችን እንዲደርስ እያደረግን መስራታችንን እንቀጥላለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ 16.9K views20:30