Get Mystery Box with random crypto!

hotie preparatory

የቴሌግራም ቻናል አርማ hotiepreparatory — hotie preparatory H
የቴሌግራም ቻናል አርማ hotiepreparatory — hotie preparatory
የሰርጥ አድራሻ: @hotiepreparatory
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.66K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-11-24 16:58:38 የትምህርት ቤታችን ሴት መምህራን!
540 views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 09:09:01 ቀን 13/03/2015 ዓ.ም
አስቸኳይ የጥሪ ማስታወቂያ
ለ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለወሰዳችሁ መደበኛ ፣ ድጋሚ ተፍታኝ እና የማታ(የግል) ተፍታኝ ተማሪዎች በሙሉ
የ2014 ዓ.ም የትምህርት መስክና የዩኒቨርስቲ ምርጫ በትምህርት ቤት ደረጃ የሚሞላው ከህዳር 13_14/03/2015 ዓ.ም ብቻ መሆኑን እየገለፅን ማንኛውም ተማሪ :-
1. ህዳር 13/03/2015 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በአካል ትምህርት ቤት በመገኘት ገለጻ በመውሰድ ህዳር 14/03/2015 ዓ.ም ከጧቱ 2፡00 ላይ ትምህርት ቤቱ አይሲቲ ትምህርት ክፍል ገቢ ማድረግ አለበት፡፡
2.ማንኛውም ተማሪ ፎርም ከሞሏ በሗላ በምንም አጋጣሚ መቀየር ስለማይቻል ቀድሞ ከቤተሰብ ጋር በመመካከር ትክክለኛ የዩኒቨርስቲ ምርጫ ከ1-40 ሁሉንም ዩኒቨርስቲ እና ፌልድ መሙላት አለበት፡፡
3.በሚዘጋጀው ቅፅ ላይ ትክክለኛሙሉ ስም ከነ አያት በእንግሊዝኛ Capital Letter መፃፍ
4. Registration Number በትክክል መፃፍ
5.ሁሉንም መረጃዎች ያለ ምንም ስርዝ ድልዝ መፃፍና መጨረሻ ላይ የተማሪው ፊርማ ማስቀመጥ
6.የመሙሊያ ቅፅ ትምህርት ቤቱ ባዘጋጀው ብቻ በመሆኑ ከትምህርት ቤት መውሰድ አለበት
7.በውክልና መረጃ የማይሞላ መሆኑ ይታወቅ።
8.በተባለው ዕለት መጥቶ ዩኒቨርሲቲ እና ፌልድ ያልሞላ ተማሪ ሙሉ ኃላፊነቱን ተማሪ የሚወስድ መሆኑ ይታወቅ ፡፡
ማሳሰቢያ :- ሁሉም ተማሪዎች መረጃው እንዲደርሳቸው ለምታውቋቸው ጓደኞቻችሁ እና ቤተሰብ እንድታስተላለፉ ትምህርት ቤቱ ያሳውቃል ።
የት/ቤቱን መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳችሁ የት/ቤቱን የቴሌግራም ቻናላችንን @hotiepreparatory ይቀላቀላሉ
1.2K views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 10:53:23 # የሰኮላርሽፕ ማስታወቂያ ዕድሜያቸዉ ከ18-24 ለሆኑ ሴት አመልካቾች
በራሽያ ሃገር የሚገኛዉ ‘’Special Economic Zone "Alabuga"’’ የተሰኘ ተቋም ዕድሜያቸዉ ከ18-24 ለሆኑ ሴት ተማሪዎች የስልጠና እድል ስላመቻቸ ፍላጎቱ ያላችሁ ከታች በተቀመጠዉ ማሰፈንጠሪያ እስከ ህዳር 02/03/2015 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡
(https://forms.gle/zsFV5HqVoGDufr2v8)
ትምህርት ሚኒስቴር!
558 views07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-19 18:00:44 ቀን 09/02/2015
ማስታወቂያ
የሆጤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ የመማሪያ መጽሐፍ የመመለሻ ፕሮግራም ከዚህ በታች ባለው መሰረት ት/ቤት በመገኘት እንድትመልሱ እያሳወቀ ከፕሮግራሙ ውጭ የምትመጡ ቅጣት ያለው መሆኑን ከወዲሁ ት/ቤቱ ይገልጻል፡፡
የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ
ጥቅምት 10 እስከ 11/2015ዓ.ም ድረስ
የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች
1- ROOM 1-2 ማክሰኞ ጥቅምት 15/2015ዓ.ም
2- ROOM 3-4 ረቡዕ ጥቅምት 16/2015ዓ.ም
3- ROOM 5-6 ሐሙስ ጥቅምት 17/2015ዓ.ም
4- ROOM 7-8 ዓርብ ጥቅምት 18/2015ዓ.ም

የት/ቤቱን መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳችሁ የት/ቤቱን የቴሌግራም ቻናላችንን @hotiepreparatory ይቀላቀላሉ
1.5K views15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 13:16:28 ቀን 04/02/2015
ማስታወቂያ
የሆጤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2013 እና
የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
የሆጤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2013 እና
የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በ2015 ዓ.ም ለሀገር
አቀፍ ፈተና ለመፈተን ምዝገባ ያከናወናችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ
ተማሪዎች ሁናችሁ የመፈተኛ ካርዳችሁ ግን የማህበራዊ
ሳይንስ ተብሎ የመጣላችሁ ከት/ቤት ደብዳቤ በመያዝ መፈተን
የምትችሉ በመሆኑ ት/ቤት በመምጣት ደብዳቤ እንድትወስዱ
ት/ቤቱ ያሳውቃል፡፡
የት/ቤቱን መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳችሁ የት/ቤቱን
የቴሌግራም ቻናላችንን @hotiepreparatory ይቀላቀላሉ
1.8K views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 10:33:23 ቀን 03/02/2015
ማስታወቂያ
የሆጤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ
እንደሚታወቀው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ በኋላ የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለት/ቤቱ የበጎ አድራጎት ክበብ በየዓመቱ በመስጠት ይታወቃሉ፤ በዚህ ዓመትም የደንብ ልብሳችሁን በማጠብና በመተኮስ ለት/ቤቱ ገቢ እንድታደርጉ ትብብራችሁን ትጠየቃላችሁ፡፡
የት/ቤቱን መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳችሁ የት/ቤቱን የቴሌግራም ቻናላችንን @hotiepreparatory ይቀላቀላሉ
1.8K viewsedited  07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 21:38:20 ቀን 30/01/2015
ማስታወቂያ
የሆጤ  አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2013 እና የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች  በሙሉ
የሆጤ  አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2013 እና የ2014ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች  በ2015 ዓ.ም ለሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ምዝገባ ያከናወናችሁ  የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች  ቅዳሜ ጥቅምት በ05/02/2015ዓ.ም ከጧቱ 1:00 ላይ ት/ቤት እንትገኙ እያሳወቀ በዕለቱ የማይገኝ ተማሪ ለሚደርስበት መጉላላት ኃላፊነቱን ተማሪው የሚወስድ መሆኑን ት/ቤቱ ያሳውቃል ።
በተጨማሪም 1.ሁሉም ተማሪ በተጠቀሰው ዕለት ሰዓት አክብሮ ት/ቤት መገኘት ይኖርበታል ።
2. በግልና በቡድን የሚደረግ ጉዞ ተቀባይነት የለውም ።
3.ለአንድ ተፈታኝ ተማሪ የመጓጓዣ ወጪ ለደርሶ መልስ 70(ሰባ ብር) እያንዳንዱ እንድታዘጋጁ
4.የ2014ዓ.ም መደበኛ ተማሪዎች የደንብ ልብስ ፣የት/ቤቱን መታወቂያና የመፈተኛ ካርድ መያዝ ይኖርባችኋል ።
5.የ2013ዓ.ም እና የማታ ተማሪዎች የቀበሌ መታወቂያና የመፈተኛ ካርድ መያዝ ይኖርባችኋል ።
በዕለቱ ወደ መፈተኛ ዩኒቨርስቲ የምትሄዱ በመሆኑ አስፈላጊውን ቁሳቁስ ይዛችሁ እንድትገኙ እያሳሰበ የፎቶግራፍ እና የመፈተኛ ካርድ ስም ስህተት ያጋጠማችሁ ተማሪዎች ካላችሁ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ በመያዝ እንድትመጡና ዩኒቨርስቲ ውስጥ የማስተካከያ ፎርም የምትሞሉ መሆኑን ት/ቤቱ  ያሳውቃል ።

የት/ቤቱን መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳችሁ የት/ቤቱን የቴሌግራም ቻናላችንን @hotiepreparatory ይቀላቀላሉ
382 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 16:22:13 ማስታወቂያ ከትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 30/2015 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል፡፡
ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን እና የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ መደረጉን በአክብሮት እየገለጽን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አዉቃችሁ በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንድትከታተሉ እናሳስባለን።
ትምህርት ሚኒስቴር !
798 views13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ