2022-08-31 22:28:53
#አፍላ ፍቅር
ፀሃፊ ካሊድ ታረቀኝ (ye umi)
Part ❷0
በዚህ መሃል የሃናን አባት በተራቸው ሊሰግዱ ነው መሰለኝ ሲመጡ ተገጣጠምን፡ የሃናን አባት ምግብ በአፋቸው ለረዥም ሰአታት ያህል እንዳልዞረ እንኩቶ ሆኖ በነጭ ቀለም ዙሪያው የተለውሰው ከንፈራቸው ይናገር ይዟል። ለዚህ ሁሉ ነገር በህግም ቢሆን ተጠያቂዎቹ እነ አምሪ ናቸው ባይነኝ።
የሰውልጅ ኑሮን እራሱ የሰው ልጅ ለምን ለማናገት ይቸኩላል፡ ማገናዘብ የሚባለው ነገር የት ደረሰ።
እነ አምሪ ይኼኔ ሲስቁና ሲጫወቱ ከቤተሰብ ጋር አድረዋል፡ ያቺ ምስኪን ግን...። ምናልባት ዛሬ ትምህርት ቤት ከገቡ የሃናን ስልክ አለመስራቱና ከክፍሉ ውስጥ አለመገኘቷ ከነሱ መሰወሯ ወደ ቤቷ ሊያስኬዳቸው ይችላል ብዬ እገምታለሁ ፡
ከጎረቤት ወይም ከአካባቢው ነዋሪዎች ውስጥ የተፈጠረውን የሰማ ካለ ስለሃናን መጥፋት ሹክ ይላቸው ይሆናል፡
ያው በመደናገጥ ችግሩ የተፈጠረው በእነሱ ምክንያት መሆኑን በወቅቱ ሊዘነጉት ይችላሉ ባይ ነኝ፡ ግና በነሱ ምክንያት መሆኑን ቆይተውም ቢሆን የተገነዘቡ ጊዜ በሰሩት ድርጊት አፍረው ከመፀፀት መንደር የሚገቡ ይመስለኛል
ከዚያ ውጭ ነገሮች መንገድ ቢቀይሱ ማለትም ፡አላህ ይጠብቃትና ሃናንን ከዚህ በኋላ ከዱኒያው አለም ላይ ካጣናት በሞት ከተነጠኩ ሙሉ ለሙሉ፡ የሃናን ገዳይ እነሱ እንደሆኑ ለሚመለከተው አካል ሁሉ መናገሬ አይቀርም፡፡
እኔምለው ግን ይህችን ሁለት ቀን እዚህ ሆስፒታል ስገባ የሃናንን እናት አልተመለከትኩም። መቼም መሰገጃ አቀባይዋና እንድሰግድ አዛዧ ለሃኑ ታላቅ እህቷ ትሆናለች እንጂ መቼም....።
ምናልባት ግን እናቷ ድንጋጤ የማይችሉ ሁነው ሳይነገራቸውም ቀርቶ ቢሆንስ እስካሁን ያላየኋቸው ፡እረ ወደሃናን መገኛስ መች አቀናሁና እዛ ተቀምጠው ቢሆንስ ውስጥ መግባት ባይቻልም እውጭ ላይ።
እንደጠረጠርኩት የሃናንን አባት ለሶላት ነበር ሲጓዙ የተገጣጠምነው።
ለልጅቷ ከማል ስልክ አላነሳ አለኝ በቃ ሰግጄ መጣሁ ሲሉ ከእኔ ጋር ሰላምታ ተለዋውጠው ወደ መስገጃው ቦታ አብረውኝ ተጓዙ፡ ከሃናን ውጭ አንዳች ነገር ሃሳብ ሆናባቸዋለች።
ኡዱ አድርጌ የሃናን አባት ከጎኔ ሌላ አንድ ሰው ኢማም ሁኖ ከፊት በመቆም ከሌሎች ሰዎች ጋር ጀመአ በመፍጠር ዙሁርን ሰገደን፡
ከሰላት በኋላ ከጎኔ ስለተቀመጡት የሃናን አባት አስብ ጀመር፡
ትንሽ ልብሳቸው በላቸው ላይ ወደ ማደፋ እየቃጣው እንዳለ አስተዋልኩ፡ እንዴት ሁኖ የሃናን እንደዛ መዘነጥ እኮ ኑሯቸውን በኮተታ ኮተት ከሚያሸበርቁት መካከለኛ ወይንም ሃብታም ከሚባሉ ሰዎች ወይንም ቤተሰብ ውስጥ የወጣች ነበር የሚያስመስለው፡ እኔ እንደዛ ነው እስካሁን በክፍል ውስጥ በምታደርገው እንቅስቃሴ የማስባት። ለነገሩ የሰውልጅ ቀርበው ሳያዩት በግምት ባዩት መለፍለፉ አግባብነት የለውም።
ከሰላቱ በኋላ ሃናን ወዳለችበት አቅጣጫ ከአባቷ ጋር አቀናን እንደደረስን በቦታው መስገጃ የሰጠችኝ ልጅ ስለነበረች መስገጃውን መልሼላት በቦታው ካለ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡ ወደ ውስጥ መግባት አይቻልም ሌላ ታማሚ ያለባቸው ሴት ወንድ ወጣቶች በየቦታው ተቀምጠዋል በየመሬቱ ካርቶን አንጥፈው ተኝተዋል። እዚህ ስትመጣ አፊያ ምን ያህል ውድ ስጦታ እንደሆነ ትገነዘባለህ። አሁንም የሃናን እናት ግን ከዚህ ቦታ የሉም።
የሃናን አባት ከእኔ ጋር ከመጡ ጀምሮ ወዲያ ወዲህ በመንጎራደድ ስልክ በመደጋገም ይደውላሉ ግን ሲያወሩ አይደመጥም፡ ምናልባት ቅድም ለልጅቷ ያሏት አካል አሁንም ስልኩን ሊያነሳ ፍቃደኛ አልሆነላቸውም መሰለኝ።
በዚህ መሃል ልጅቷ ከጎኔ መታ ተቀመጠች፡ የሃናን አባት ወደ ውጭ ስለወጡ ወሬዋን ከእኔ ጋር አድርጋች።
ጥቂት በሃናን ጉዳይና በሆስፒታሉ ዙሪያ ካወራን በኋላ፡ በመሃል
አንቺ እህቷ ነሽ? ስል ጠነኳት።
አዎ ታላቅ እህቷ ነኝ አንመሳሰለም?
ለማንኛውም አሚና አባላለሁ ስትል ስሟን አስከተለች።
እኔ የክፍል ጓደኛዋ ነኝ አቡበክር እባላለሁ።
እ አወኩህ አንድ ቡድናችሁ?። እንዴት አወቀችኝ በሚል እየተወዛገብኩ
አዎ ምነው?
አይ እቤት አንዳንዴ በጫወታ መሃል ሃናን ስምህን ታነሳ ነበር።
ሰው ማማት ሃራም አይደል እንዴ። አልኩ ውስጤ እየሳቀ።
እሷም ምላሽ ስለሌላት ፈገግ አለች በዝምታ።
እኔም ዝምታዋን ተንተርሼ በሃሳብ ተጓዝኩ ሃኑ ትወደኛለች ማለት ነው? ስል እራሴን ጠየኩ።
በዚህ መሃል የሃናን አባት ከሄዱበት ተመልሰው መጡ። ወደ እኛ እንደተጠጉ
አሚ ሲሉ ንግግራቸውን ለልጃቸው አሰሙ።
ወዬ አባ።
ከማል አልፈቅድልህም አለኝ ባክሽ። እንደከፋቸው ፊታቸው ያስታውቃል።
እና?።
ማንም ሳይነካቸው የሃናን አባት በጩኸት ያባረኝ በቃ ለልጄማ አላንስም ሲሉ ሆድ ብሷቸው እንባቸው በፂማቸው በኩል እየተንሸራተተ ከጃኬታቸው ላይ ይንጠባጠብ ጀመረ። ጩኸታቸው በጣም አስደንግጦኛል፡
ምን እንደተፈጠረ አላውቅም ግን ሆዴን ባር ባር ይለው ጀመር፡ ከማል የተባለው ሰው ግን ለሃናን አባት አሰሪያቸው ይመስለኛል ምክንያቱም አከራያቸው ቢሆን ያባረን እንጂ ያባረኝ አይሉም ስለዚህ ነገሩ የስራ ጉዳይ ይመስለኛል።
አሚና የአባቷን ፊት ፊት እያየች ጠንከር ብላ ንግግሯን ቀጠለች፡
በቃ አባ አንተ ሳተኛ ነው ያደርከው
እና አሁን እዚህ ተኛ የዛሬውን ለብቻዬም ቢሆን እኔ አድራለሁ አንተ እረፍት አድርግና ምሳ በልተኽ ስራህ ግባ።
ብላ ከመቀመጫዋ ተነስታ አባቷን ለማጠንከር በሚመስል መልኩ አቀፈች።
አንዳንዴም ሃብታም ቀልብ የለውም የሚባለው የእውነት ነው እንዴ አስባለኝ፡ መቼም ልጅ ታሞባቸው መሆኑን ሳይነግሩት አይቀርም እንዴት ሰው ሰው መሆን አቃተው ያውም ከማል የተባለው አሰሪያቸው እኮ ሙስሊም ነው፡ ብቻ የዚህች አለም አንዳንድ ሰውነን ባዮች ያስገርማሉ ከሰውነት ጥግ እየወጡ ሰው ነን።
ከአሚና ጋር ስንጫወት ቆይተን ማምሻውን ወደ እቤት ሄድኩ፡ ዛሬ ሄኒ እቤት ይገባል ብዬ እገምታለሁ ነገር ግን ተነግሮኝ ባለመጠየቄ አፍሬያለሁ።
ወደ እቤት እንደገባሁ እናቴን ከተቀመጠችበት የጠዋቱን ጉዳይ በሚያስረሳ መልኩ ግጥም አድርጌ ጉንጮቿን በመሳም አለፍ ብዬ ወደ ክፍሌ ልገባ ስል፡
የጠዋቱን ነገር እየጠበኩ ነበር አለችኝ?
ስጋቷን ስለተረዳሁ ፈገግ በማለት አይ እማዬ አላነበብኩትም።
የእውነትህን ነው፡ አቡ እኔ አሁን እውነቱን ልነግርህ ዝግጁ ነኝ አንተን ማጣት አልፈልግም፡ አንብበከውም ከሆነ እውነቱን ንገረኝና ስለተፈጠረው ነገር ሳልደብቅህ ልንገርህ። አለችኝ ነገሩ በጣም እንዳስጨነቃት ከንግግሯና ከአኳኋኗ ስለተረዳሁ ወደ ኋላ በመመለስ ከጎን ተቀመጥኩና፡
እማዬ የእውነቴን ነው አልዋሸሁም ከአንድ ወረቀት ውጭ አላነበብኩም እስኪ ምንድነው ነገሩ ከወረቀቱ ይልቅ ስለ እህቴ ሶፊ ካንቺ አንደበት የተፈጠረውን ልስማ፡
እማዬ ጥቂት መሬት መሬቱን ከተመለከተች በኋላ ጉሮሮዋን በመጠራረግ ስለ እህቴ ሶፊ መናገር ጀመረች
ወቅቱ የአዲስ አበባን ነዋሪን በተለይ ወጣት ተማሪን በዚና(የሀራም ግንኙነት) መአበል....
ክፍል ❷➊ ይቀጥላል
ሶፊ ማናትስ የትናትስ?????
https://t.me/hannyTube
130 views19:28