ከአላህ ሱብሀነሁ ወተአላ ዉጭ በሆነ ነገር የተሞላ ልብ ሁሉ ባዶ ነው !!! { وَأَصْبَحَ فُؤَادُ أُمِّ مُوسَىٰ فَٰرِغًا } «የሙሳም እናት ልብ ባዶ ሆነ » 【አል ቀሰስ 10】 የሙሳ እናት ሙሳን ከማስታወስና ስለእሱ ከማሰብ ውጭ ሌላ ልቧን የሞላው ነገር አልነበረም ። {إِن كَادَتْ لَتُبْدِى بِهِۦ لَوْلَآ أَن رَّبَطْنَا عَلَىٰ قَلْبِهَا لِتَكُونَ مِنَ ٱلْمُؤْمِنِينَ} « ከምእምናን ትሆን ዘንድ በልቧ ላይ ባላጠነከርን ኖሮ ልትገልጸው ቀርባ ነበር፡፡» አላህ በልቧ ላይ ያለውን ኢማን ባያፀናላት ኖሮና ባትጠናከር … ሙሳ ልጇ እንደሆነ በተናገረች ነበር … ይህም የማንኛውም ባዶ ልብ ሁኔታ ነው ። ባጋጠመመው ችግርና መከራ በፍርሀት ሊበር ይደርሳል ። በአላህ እንደማመንና እንደመተማመን ሊያፀናውና ሊያጠነክረው የሚችል ነገር የለም። ለእነዚያ ለተጨነቁና ግራ ለተጋቡ ልቦች ከዚህ በአንደበት ውስጥ ከሚሰርፀው ኢማን በስተቀር መረጋጋትና ስክነትን የሚያሰፍን ነገር የለም ። ይ ላ ሉን share ┏━ ━━━━ ━┓ @Halal_Fonqaa ┗━ ━━━━ ━┛ 234 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 20:09