እውቁ አሜሪካዊ ድምጻዊ አር ኬሊ በጾታዊ ጥቃት ወንጀል የ30 ዓመት እስር ተፈረደበት ታዋቂው የአሜረካዊ የአር ኤንድ ቢ አቀንቃኝ አር ኬሊ በአሜሪካ ፍርድ ቤት የ30 ዓመት እስር እንደተፈረደበት ተነግሯል። የ55 ዓመቱ ሙዚቀኛ ባሳለፍነው መስከረም ወር ላይ ነበር በወሲብ ንግድ፣ በህፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት፣ በአፈና እና ሌሎች ከወሲብ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ተከሶ ፍርድ ቤት የቀረበው። በዚህም ፍርድ ቤቱ ትክክለኛ ስሙ ሮበርት ሲልቪስተር ኬሊ በተባለው ድምጻ ላይ የ30 ዓመት እስር የፈረ ሲሆን፤ ይግባኝ ማለት መብት እንዳለውም አስታውቋል። 57 views07:58