2022-04-04 14:27:42
ኢየሱስ ዳግመኛ ይመጣል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ የሚያወራው ስለ ክርስቶስ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ስለማንም ታሪክ ቢያነሳ የሚያመለክተው ስለ ክርስቶስ። ለዛ ነው ኢየሱስ ስናገር መጽሐፍት ሁሉ ስለ እኔ ይናገራሉ ያለው።
ሙሉ ታሪክ ስለ ክርስቶስ ይናገር እንጂ ታሪኮቹ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ በእግዚአብሔር አምሳያ የተጠፈጠረውን የሰውን ልጅ የማዳን ጉዞ ያመለክታሉ።
ከዚህ በመቀጠል በኖኅ መርከብ ታሪክ ላይ ስለ ክርስቶስ ምስል የሚናይበት ይሆናል። አጠቃላይ የብሉይ ኪዳን ታሪኮች የአዲስ ኪዳን ጥላ ናቸው። ሙሉውን ነጸብራቅ የሚናገኘው በአዲስ ኪዳን ውስጥ ነው።
ክፍል አንድ በሰው ልጅ አመጽ ምክንያት እግዚአብሔር በኖኅ ዘመን እንደተቆጣና በቁጣውም ምክንያት ምን ለማድረግ እንደቆረጠ በጥቅቱ ለማየት ሞክረናል። ለማስታወስ ያኪል
“አጸያፊነቱም የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን ወለዱላቸው ይሄ ተግባር የእግዚአብሔርን ቁጣ እጅግ ጨመረ። እግዚአብሔርም የሰውን ልጅ በመፍጠሩ በጣም ተጸጸተ።”
ምክንያቱም የሰው የልቡ ሀሳብ ምኞትም ሁልግዜ ፈጽሞ ክፉ እንደ ሆነ ስላየ። ከዛ የተነሳ እግዚአብሔር በልቡም አዘነ።
እግዚአብሔር የጽድቅ ረሃብተኛ አምላክ ነው። አካሄዱን ከእርሱ ጋር የሚሄድ ሰው ብቻ የእግዚአብሔርን ልብ ያሸንፈዋል። ከእርሱ ጋር የሚሄድ ባይኖር ብቻውን የሚቆም አምላክ ነው።
በኖኅ ዘመን በዓለም የሚኖር ሰው ሁሉ አመፀኛ ሲሆን
“እግዚአብሔርም ኖኅን አለው። አንተ ቤተሰቦችን ሁሉ ይዘህ ወደ መርከብ ግባ፤ በዚህ ትውልድ በፊቴ ጻድቅ ሆነህ አይቼሃለሁና።”
ከንጹሕ እንስሳ ሁሉ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት፥ ንጹሕ ካልሆነ እንስሳም ሁለት ሁለት ተባትና እንስት፥ ከሰማይ ወፍ ደግሞ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት እያደረግህ በምድር ላይ ለዘር ይቀር ዘንድ ለአንተ ትወስዳለህ። ከሰባት ቀን በኋላ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ አዘንባለሁና፤ የፈጠርሁትንም ፍጥረት ሁሉ ከምድር ላይ አጠፉለሁና።ኖኅም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሁሉ አደረገ።
በአዲስ ኪዳን ላይ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ካደረገው ጋር ታሪኩን ሲናይ በጣም በተለየ መንገድ ነው።
በኖኅ ዘመን ሰው ሁሉ አመፀኛ ሳለ አመፀኞችን ሁሉ ለማዳን አልሄደም። ይልቅ በጽድቅ የሄደውን ኖኅንና ቤተሰቦቹን ብቻ በራሱ የጽድቅ መንገድ አዳነ።
በአዲስ ኪዳን ግን ሙሉ ታሪኩን ሲናጠና ከሰው ልጆች ምንም አይነት የጽድቅን ሕይወት አልፈለገም ምክንያቱም የሰው ልጅ ጽድቅ የመርገም ጨርቅ ስለሆነ። በዛ ምክንያት የዓለም ሁሉ ሕዝብ የሚድንበትን ብቸኛ መንገድ አዘጋጀ እሱም በልጁ በክርስቶስ ብቻ በማመን የሚገኝ የጽድቅ ሕይወት ነው።
በእርግጥ በኖኅ ዘመንም ኖኅ ጻድቅ ሆኖ ሳለ የመዳኛ መንገድ እግዚአብሔር ነው ያዘጋጀው እሱም መርከብቱን እንዲሰራ ነገረው።
ያቺ መርከብ ብቻኛ የመዳኛ መንገድ ነበረች። መርከብቱም የዛሬውን ብቸኛ የመዳኛ መንገድ የሆነውን ክርስቶስን ትውክላለች።
መርከቢቱ ተሰርታ ሲታልቅ በመኃሉ ላይ አንድ በር ብቻ ነበራት። ኖኅና ቤተሰቦቹ እንዲሁም የተመረጡት እንስሳት የገቡበት። ያቺ በር ወደ መንግስተ ሰማይ መግቢያ በር ክርስቶስ ብቻ መሆኑን ትወክላለች።
“በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።” ዮሐ 10:9 – 10
“በመጨረሻም ሥጋ ካለው ሁሉ የገቡትም ተባትና እንስት እግዚአብሔር እንዳዘዘው ገቡ፤ እግዚአብሔርም በስተ ኋላው ዘጋበት።” ዘፍ 7:16
የምህረት ግዜ ገደብ አለው። አንድ ቀን ዛሬ የተከፈተው በር የምዘገባት ግዜ ይመጣል።
ግዜው ከመቼም ይልቅ የክርስቶስ መምጫው የቀረበበት ግዜ ላይ ነን። ቃሉ ከነገረን ምልክቶች ሁሉም ማለት ይቻለል ፍፃሜውን አግኝቱሃል። አሁን የቀረው የእርሱ መምጣት ብቻ ነው። ለኛ በክርስቶስ ላመነው ይመጣልናል፤ ላላመኑት ደግሞ ይመጣባቸዋል።
በኖኅ ዘመን የጥፋት ውሃ እስኪመጣ ሰወች ያገቡ ይጋቡ ነበር። የየእለት ተግባራቸውን ያደርጉም ነበር። የመንቂያን ድምጽ የሰማው ኖኅ ግን መርከብቱን ይሰራ ነበር።
ዛሬም እንደ ኖኅ ዘመን ወንጌል እየተሰበከ ነገር ግን ብዙወች ልባቸውን ከእግዚአብሔር ያራቁበት ግዜ ነው።
እንደ ክርስቲያን ከመቸም ግዜ በላይ ሙሹራዋ ባሏን ተዘጋጅታ እንደምትጠብቅ ተዘጋጅተን የሚንጠብቅበት ግዜ አሁን ነው። የክርስቶ ዳግም ምጻት በእርሱ ያላመኑት ላይ ሊፈርድ እና በእርሱ ያመነውን ደግሞ ሊወስደን ነው።
የክብር ታስፋችን ኢየሱስ ይመጣል።
የጌታ ሰላምና ፀጋ ይብዛላቹ።
@tebazushows
@tebazushows
546 viewsedited 11:27