Get Mystery Box with random crypto!

Go to the world/ሂዱ ወደ ዓለም የወንጌል አገልግሎት

የቴሌግራም ቻናል አርማ gototheworld1 — Go to the world/ሂዱ ወደ ዓለም የወንጌል አገልግሎት G
የቴሌግራም ቻናል አርማ gototheworld1 — Go to the world/ሂዱ ወደ ዓለም የወንጌል አገልግሎት
የሰርጥ አድራሻ: @gototheworld1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 937
የሰርጥ መግለጫ

አላማችን ትውልዱን ከሀሰት አስተምህሮ መታደግና እውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮትን በማስተማር በየአመቱ GO በሚል መሪ ቃል ትውልዱን ወደ አለም ሁሉ በወንጌል እንዲደርሱ ማሰማራት ነው።
በዚህ አገልግሎት ከእኛ ጋር ለማገልገል ከፈለጉ በዚህ ስልክ ቁጥሮች በመደወል መመዝገብ ይችላሉ!!
251916091904
251934140013
እንዲሁም ይህን የወንጌል አገልግሎት በገንዘብ ለመደገፍ..

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-21 21:58:51 "፤ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 26: 41)
Join us
@gototheworld1
@gototheworld1
40 viewsTebazu Bekele, 18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 09:37:37
https://t.me/gototheworld1
60 viewsTebazu Bekele, edited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 09:37:35
https://t.me/gototheworld1
54 viewsTebazu Bekele, edited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 01:17:22 ወንጌል ለምን እንመሰክራለን?

  ሰዎች ሁሉ ከእግዚአብሄር ጋር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ባለ እምነት ታርቀው የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ ካለን ልባዊ ፍላጎት  የተነሣ ወንጌልን እንሰብካለን። ሰዎች የምስራቹን ካልሰሙ በኃጢአታቸው ምክንያት የዘላለም ሞትን ይሞታሉ። የእግዚአብሄርም ቁጣ በአለማመናቸው ምክንያት በእነሱ ላይ ይኾናል። የምንመሰክርበትን አንኳር ምክንያት በሁለት መንገድ ማስቀመጥ እንችላለን።  ሰዎችን በክርስቶስ ፍቅር ስለምንወድዳቸው ወንጌልን እንነግራቸዋለን። “..የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል..” (2ቆሮ.5፡14)። የተካፈልንውን የክርስቶስ ፍቅር ፣ ያገኘንውን የዘላለም ህይወት ለሰዎች ማካፈል ደስታችን ነው (1ዩሐ.1፡1-4)። ወንጌልን መመስከር ከፍቅር የተነሣ የምናደርገው ተግባር ነው። ሰዎች በኃጢአታቸው እንዳይጠፉ፣ የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ ስለምንፈልግ ወንጌልን እንመሰክራለን።

ሌላው ምክንያት ወንጌልን መመስከር ከጌታ የተሰጠን ትዕዛዝ ስለሆነ እንመሰክራለን። የምስክርነት ተግባር በአራቱም ወንጌላት እና በሐዋርያት ስራ ተጠቅሷል (ማቴ.28፡18-20፣ ማርቆ.16፡15፣ሉቃ.24፡47 ፣ ዩሐ.20፡21 ሐዋ.1፡8)። ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ለማድረስ ለሆነው አገልግሎት በእግዚአብሄር  ተልከናል።

በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሄር ጋር የተራቁ ሰዎች ሁሉ ሌሎች እንዲታረቁ የማስታረቅን አገልግሎት ተቀብለዋል፣ “እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን..”(2ቆሮ.5፡19-20)። ይሄ አገልግሎት በእግዚአብሄር ለሁላችንም ተሰጥቶናል።

ከጨለማው ዓለም የጠራንን፣ የዘላለም ህይወት የሰጠንን፣ ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ ያልተገባንን ቸርነት ያደረገልንን የጌታን በጎነት ለሌሎች መናገር የምድር ቆይታችን አገልግሎት ነው። ሐዋርያው ጴጥሮስ ስለዚህ አገልግሎታችን እንዲህ ብሎ ይናገራል፣ “እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ..”(1ጴጥ 2፡9-10)።
Join us
  @gototheworld1
@gototheworld1
62 viewsTebazu Bekele, edited  22:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 00:47:11
አስደሳች ዜና
Go to the world
ሂዱ ወደ ዓለም የወንጌል አገልግሎት
አላማችን ትውልዱን ከሀሰት አስተምህሮ መታደግና እውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮትን በማስተማር በየአመቱ GO በሚል መሪ ቃል ትውልዱን ወደ አለም ሁሉ በወንጌል እንዲደርሱ ማሰማራት ነው።
በዚህ አገልግሎት ከእኛ ጋር ለማገልገል ከፈለጉ በዚህ ስልክ ቁጥሮች በቴሌግራም ውስጥ ያናግሩን እንዲሁም በመመዝገብ በቅርብ ቀን በቴልግራም ቻናላችን መሰጠት የሚጀምረውን የወንጌል ስልጠና መከታተል ይጀምሩ!!
+251916091904
+96170286091
አሁኑኑ ይመዝገቡ!!
በአንድ ነፍስ አንድ ነፍስ!
Join Us telegram
https://t.me/gototheworld1
https://t.me/gototheworld1
53 viewsTebazu Bekele, edited  21:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 23:58:59 አስደሳች ዜና
አላማችን ትውልዱን ከሀሰት አስተምህሮ መታደግና እውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮትን በማስተማር በየአመቱ GO በሚል መሪ ቃል ትውልዱን ወደ አለም ሁሉ በወንጌል እንዲደርሱ ማሰማራት ነው።
በዚህ አገልግሎት ከእኛ ጋር ለማገልገል ከፈለጉ በዚህ ስልክ ቁጥሮች በመደወል መመዝገብ ይችላሉ!!
+251916091904
+96170286091
ይመዝገቡ!!
በአንድ ነፍስ አንድ ነፍስ!
https://t.me/gotoworld1
https://t.me/gotoworld1
69 viewsTebazu Bekele, edited  20:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 08:20:34 "፤ በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።"
(የያዕቆብ መልእክት 1: 12)
Join Us
@gototheworld1
@gototheworld1
474 viewsedited  05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-08 20:18:06 "፤ ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 54: 13)
Join Us
@tebazushows
@tebazushows
448 views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-04 14:27:42 ኢየሱስ ዳግመኛ ይመጣል? 

መጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ የሚያወራው ስለ ክርስቶስ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ስለማንም ታሪክ ቢያነሳ የሚያመለክተው ስለ ክርስቶስ። ለዛ ነው ኢየሱስ ስናገር መጽሐፍት ሁሉ ስለ እኔ ይናገራሉ ያለው። 

ሙሉ ታሪክ ስለ ክርስቶስ ይናገር እንጂ ታሪኮቹ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ በእግዚአብሔር አምሳያ የተጠፈጠረውን የሰውን ልጅ የማዳን ጉዞ ያመለክታሉ። 

ከዚህ በመቀጠል በኖኅ መርከብ ታሪክ ላይ ስለ ክርስቶስ ምስል የሚናይበት ይሆናል። አጠቃላይ የብሉይ ኪዳን ታሪኮች የአዲስ ኪዳን ጥላ ናቸው። ሙሉውን ነጸብራቅ የሚናገኘው በአዲስ ኪዳን ውስጥ ነው። 

ክፍል አንድ በሰው ልጅ አመጽ ምክንያት እግዚአብሔር በኖኅ ዘመን እንደተቆጣና በቁጣውም ምክንያት ምን ለማድረግ እንደቆረጠ በጥቅቱ ለማየት ሞክረናል። ለማስታወስ ያኪል 

“አጸያፊነቱም የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን ወለዱላቸው ይሄ ተግባር የእግዚአብሔርን ቁጣ እጅግ ጨመረ። እግዚአብሔርም የሰውን ልጅ በመፍጠሩ በጣም ተጸጸተ።”

  ምክንያቱም የሰው የልቡ ሀሳብ ምኞትም ሁልግዜ ፈጽሞ ክፉ እንደ ሆነ ስላየ። ከዛ የተነሳ እግዚአብሔር በልቡም አዘነ። 

እግዚአብሔር የጽድቅ ረሃብተኛ አምላክ ነው። አካሄዱን ከእርሱ ጋር የሚሄድ ሰው ብቻ የእግዚአብሔርን ልብ ያሸንፈዋል። ከእርሱ ጋር የሚሄድ ባይኖር ብቻውን የሚቆም አምላክ ነው። 

በኖኅ ዘመን በዓለም የሚኖር ሰው ሁሉ አመፀኛ ሲሆን 

“እግዚአብሔርም  ኖኅን አለው። አንተ ቤተሰቦችን ሁሉ ይዘህ ወደ መርከብ ግባ፤ በዚህ ትውልድ በፊቴ ጻድቅ ሆነህ አይቼሃለሁና።”

ከንጹሕ እንስሳ ሁሉ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት፥ ንጹሕ ካልሆነ እንስሳም ሁለት ሁለት ተባትና እንስት፥ ከሰማይ ወፍ ደግሞ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት እያደረግህ በምድር ላይ ለዘር ይቀር ዘንድ ለአንተ ትወስዳለህ። ከሰባት ቀን በኋላ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ አዘንባለሁና፤ የፈጠርሁትንም ፍጥረት ሁሉ ከምድር ላይ አጠፉለሁና።ኖኅም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሁሉ አደረገ።

በአዲስ ኪዳን ላይ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ካደረገው ጋር ታሪኩን ሲናይ በጣም በተለየ መንገድ ነው። 

በኖኅ ዘመን ሰው ሁሉ አመፀኛ ሳለ አመፀኞችን ሁሉ ለማዳን አልሄደም። ይልቅ በጽድቅ የሄደውን ኖኅንና ቤተሰቦቹን ብቻ በራሱ የጽድቅ መንገድ አዳነ። 

 በአዲስ ኪዳን ግን ሙሉ ታሪኩን ሲናጠና ከሰው ልጆች ምንም አይነት የጽድቅን ሕይወት አልፈለገም ምክንያቱም የሰው ልጅ ጽድቅ የመርገም ጨርቅ ስለሆነ። በዛ ምክንያት የዓለም ሁሉ ሕዝብ የሚድንበትን ብቸኛ መንገድ አዘጋጀ እሱም በልጁ በክርስቶስ ብቻ በማመን የሚገኝ የጽድቅ ሕይወት ነው።  

 በእርግጥ በኖኅ ዘመንም ኖኅ ጻድቅ ሆኖ ሳለ የመዳኛ መንገድ እግዚአብሔር ነው ያዘጋጀው እሱም መርከብቱን እንዲሰራ ነገረው። 

ያቺ መርከብ ብቻኛ የመዳኛ መንገድ ነበረች። መርከብቱም የዛሬውን ብቸኛ የመዳኛ መንገድ የሆነውን ክርስቶስን ትውክላለች።

 መርከቢቱ ተሰርታ ሲታልቅ በመኃሉ ላይ አንድ በር ብቻ ነበራት። ኖኅና ቤተሰቦቹ እንዲሁም የተመረጡት እንስሳት የገቡበት። ያቺ በር ወደ መንግስተ ሰማይ መግቢያ በር ክርስቶስ ብቻ መሆኑን ትወክላለች። 

“በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።”  ዮሐ 10:9 – 10

 “በመጨረሻም ሥጋ ካለው ሁሉ የገቡትም ተባትና እንስት እግዚአብሔር እንዳዘዘው ገቡ፤ እግዚአብሔርም በስተ ኋላው ዘጋበት።” ዘፍ 7:16

የምህረት ግዜ ገደብ አለው። አንድ ቀን ዛሬ የተከፈተው በር የምዘገባት ግዜ ይመጣል። 

ግዜው ከመቼም ይልቅ የክርስቶስ መምጫው የቀረበበት ግዜ ላይ ነን። ቃሉ ከነገረን ምልክቶች ሁሉም ማለት ይቻለል ፍፃሜውን አግኝቱሃል። አሁን የቀረው የእርሱ መምጣት ብቻ ነው። ለኛ በክርስቶስ ላመነው ይመጣልናል፤ ላላመኑት ደግሞ ይመጣባቸዋል። 

በኖኅ ዘመን የጥፋት ውሃ እስኪመጣ ሰወች ያገቡ ይጋቡ ነበር። የየእለት ተግባራቸውን ያደርጉም ነበር። የመንቂያን ድምጽ የሰማው ኖኅ ግን መርከብቱን ይሰራ ነበር። 

ዛሬም እንደ ኖኅ ዘመን ወንጌል እየተሰበከ ነገር ግን ብዙወች ልባቸውን ከእግዚአብሔር ያራቁበት ግዜ ነው። 

 እንደ ክርስቲያን ከመቸም ግዜ በላይ ሙሹራዋ ባሏን ተዘጋጅታ እንደምትጠብቅ ተዘጋጅተን የሚንጠብቅበት ግዜ አሁን ነው።  የክርስቶ ዳግም ምጻት በእርሱ ያላመኑት ላይ ሊፈርድ እና በእርሱ ያመነውን ደግሞ ሊወስደን ነው።  

የክብር ታስፋችን ኢየሱስ ይመጣል። 

የጌታ ሰላምና ፀጋ ይብዛላቹ።
@tebazushows
@tebazushows
546 viewsedited  11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 16:09:44 ተክሎ ፡ መሄድ ፡ የአንተን ፡ ፍለጋ
ምነኛ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ቢበዛልኝ ፡ ፀጋ
አስከብሬህ ፡ ልለፍ ፡ እንደ ፡ አባቶቼ
ዓለም ፡ እና ፡ ትርፏን ፡ ሁሉን ፡ ንቄ ፡ ትቼ (፪x)

አዝ፦ ክርስትናን ፡ መኖር ፡ ዋጋ ፡ በመክፈል ፡ ነው
ግን ፡ የለብስኩት ፡ ሥጋ ፡ እጅግ ፡ ደካማ ፡ ነው
ከጐኔ ፡ በመቆም ፡ ካላበረታኸኝ
ታውቃለህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ደካማ ፡ ነኝ (፪x)

ዘወትር ፡ በፀሎት ፡ በፊትህ ፡ ልደፋ
በውስጤ ፡ ያኖርከው ፡ እሳቱ ፡ እንዳይጠፋ
ገና ፡ ላገልግልህ ፡ በኃይል ፡ ተሞልቼ
ጉብዝናዬን ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ ሰጥቼ (፪x)

አዝ፦ ክርስትናን ፡ መኖር ፡ ዋጋ ፡ በመክፈል ፡ ነው
ግን ፡ የለብስኩት ፡ ሥጋ ፡ እጅግ ፡ ደካማ ፡ ነው
ከጐኔ ፡ በመቆም ፡ ካላበረታኸኝ
ታውቃለህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ደካማ ፡ ነኝ (፪x)

ባላደራነቴን ፡ ችላ ፡ እንዳልለው
የወንጌልን ፡ ዕንቁ ፡ ለራ ፡ እንዳልጥለው
ታማኝ ፡ አድርገህ ፡ ቆጥረህ ፡ በቤትህ ፡ የሾምከኝ
ከፈተናዎቼ ፡ ፀጋህ ፡ ያሾልከኝ/ያስመልጠኝ (፪x)

ሰርክ ፡ እናይሳነኝ ፡ መንጋህን ፡ በመገብ
በሸክላ ፡ ዕቃ ፡ ውስጥ ፡ የከበረ ፡ መዝገብ
ያስቀመጥክ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ እንደ ፡ ኃይልህ ፡ ብዛት
እስከ ፡ መጨረሻው ፡ ሕይወቴን ፡ አግዛት (፪x)

አዝ፦ ክርስትናን ፡ መኖር ፡ ዋጋ ፡ በመክፈል ፡ ነው
ግን ፡ የለብስኩት ፡ ሥጋ ፡ እጅግ ፡ ደካማ ፡ ነው
ከጐኔ ፡ በመቆም ፡ ካላበረታኸኝ
ታውቃለህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ደካማ ፡ ነኝ (፪x)
424 views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ