Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ gospel_of_god — የእግዚአብሔር ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ gospel_of_god — የእግዚአብሔር ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @gospel_of_god
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.04K
የሰርጥ መግለጫ

𝘍𝘰𝘳 𝘢𝘯𝘺 𝘘𝘶𝘦𝘴𝘵𝘪𝘰𝘯𝘴 𝘰𝘳 𝘚𝘶𝘨𝘨𝘦𝘴𝘵𝘪𝘰𝘯𝘴 𝘶𝘴𝘦፡
@pray_trust_wait0

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-11-02 13:46:41 አማኞች በየእለቱ ሊያስታውሷቸው የሚገቡ ሰባት ነገሮች፦
1- እግዚአብሔር አባቴ ነው።
2- ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኜ ነው።
3- መንግተ ሰማይ ቤቴ ነው።
4- ቅዱሳት መጻሕፍት መመሪያዬ ናቸው።
5- እያንዳንዱ አማኝ ቤተሰቤ ነው።
6- ወንጌል መልእክቴ ነው።
7- የእግዚአብሔር ክብር ግቤ ነው።

__Dustin Benge

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.6K views10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 20:03:55 በክርስቶስ የቤዝዎት ሞት የቀድሞ ጠላቶች ሁሉ ታርቀዋል፤ የክፍፍል ግድግዳ ፈርሷል። በክርስቶስ አካል ውስጥ ግሪክ ወይም ይሁዲ፣ የተገረዘ ወይም ያልተገረዘ፣ አረማዊ ወይም እስኩቴስ፣ ባሪያ ወይም ጌታ፣ ወንድ ወይም ሴት የሚል ክፍፍል የለም። ከመስቀሉ ሥራ የተነሣ የክርስቶስ ማኅበረሰብ መታወቂያውም ሆነ ውቅሩ ዘር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ መደብ ወይም ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም አይደለም። እነዚህ መለያዎች በሙሉ አንጻራዊ ሆነዋል። ገዢው ፋይዳ እግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ በፈጸመው ፍጹም የዕርቅ ሥራ የተገኘው ማንነት ነው። በእርሱና በሰው፣ በሰውና በሰው እንዲሁም በሰውና በተፈጥሮ መካከል ያለውን የጥል ግድግዳ ለአንዴና ለዘላላም በማፈረስ አንድ አዲስ ሰው ፈጥሯል። “. . . ሁለቱን አንድ ያደረገ፣ የሚለያየውንም የጥል (የማይታረቅ ጠላትነት) ግድግዳ ያፈረሰ ሰላማችን እርሱ ራሱ ነውና” (ኤፌ. 2÷14-15)። አይሁድ፣ አሕዛብ፣ ወንድና ሴት፣ ባርያና ጨዋ አንድ ሆነዋል። 

ልዩነት የለም - በምድር ላይ ካሉ ማኅበረሰቦች ሁሉ፣ የክርስቶስን ማኅበረሰብ ልዩ የሚያደርገው ይኸው በመስቀሉ ሥራ ብቻ የተገኘው ማንነት፣ ሰላምና አንድነት ነው። ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሆኗል! “ከቅዱሳን ጋር የአንድ አገር ዜጋ፣ የእግዚአብሔርም ቤተሰብ አባል” የሆነው በክርስቶስ መስቀል ቤዛዊ ሥራ ነው። ይህ እግዚአብሔራዊ ቤተ ሰብነት፣ በየትኛውም መልኩ ወደ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጐራ የማይወርድ ነው።

በበዓለ አምሳ ቀን ከልዩ ልዩ ባህል፣ ነገድና ቋንቋ፣ የተሰበሰበውን ሕዝብ አንድ ያደረገው የሮም ፓለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ወይም ይሁዲነትን ጨምሮ በወቅቱ የነበሩ ሃይማኖቶች፣ ባህሎችና ማኅበራዊ ዕሴቶች አልነበሩም። መንፈስ ቅዱስ ነበር። የአዲሱ ማኅበረሰብ ገዢው መለያ ከክርስቶስ ዋጆአዊ ሥራ የተነሣ የተገኘው ማንነት ነበር። ሌሎች ምድራዊ የማንነት ልዩነቶች ሁሉ የመለያየት ግድግዳ መሆናው አብቅቷል። ስለዚህ የክርስቶስ ማኅበረሰብ ውበቱ ልዩነቱ ነው። ለእግዚአብሔር ለራሱ የተለየ ሕዝብ በሆነበት ልክ ያህል ብቻ ነው ለሌላው ሕዝብ የዕርቅና ሰላም አማራጭ የሚሆነው።

“አራቱም ሕያዋን ፍጡራን እያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፎች ነበሯቸው፤ በዙሪያቸውና በውስጣቸው በዐይኖች የተሞሉ ነበሩ፤ ቀንና ሌሊትም፦ 'ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ የነበረው፣ ያለውና የሚመጣው፤ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ' ማለትን አያቋርጡም። 'ጌታችንና አምላካችን ሆይ፤ ክብርና ሞገስ፣ ኀይልም ልትቀበል ይገባሃል፤ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና፤ በፈቃድህም ተፈጥረዋልና፤ ሆነዋልምና።'”  (  ራእይ   4 : 8 ,  11)

“እንዲህም እያሉ አዲስ መዝሙር ዘመሩ፤ 'መጽሐፉን ልትወስድ፣ ማኅተሞቹንም ልትፈታ ይገባሃል፤ ምክንያቱም ታርደሃል፤ በደምህም ከነገድ ሁሉ፣ ከቋንቋ ሁሉ፣ ከወገን ሁሉ፣ ከሕዝብ ሁሉ ሰዎችን ለእግዚአብሔር ዋጅተሃል። በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ዘመሩ፤ 'የታረደው በግ ኀይልና ባለጠግነት፣ ጥበብና ብርታት፣ ክብርና ሞገስ፣ ምስጋናም፣ ሊቀበል ይገባዋል።'”
  (ራእይ   5 : 9 ,  12 )

በርግጥ ልዩ የእግዚአብሔር ሕዝብ ከሆንን፣ የሚገዛንም ዋናው ፋይዳ ደግሞ ከሕዝብ፣ ከነገድና ከቋንቋ የተዋጀንበት ማንነት ከሆነ፣ እርስ በእርስም ሆነ ሌሎችን በብሔርተኝነት መነጽር ልንመለከት አንችልም። ከፍ ሲል ያሉትን ሦስት መዝሙሮች (ለነበረው፣ ላለውና ለሚመጣው፤ ሁሉን ለፈጠረው እንዲሁም ፍጥረትን በደሙ ለዋጀው ክርስቶስ የቀረቡ) የአምልኮው መካከል ያደረገ ክርስትናና ዘረኝት አብረው አይሄዱም።
(ተሐድሶ ይሁንልን! አሜን)

__ግርማ በቀለ (ዶ/ር)

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.1K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 09:39:38 "ተሐድሶ አራማጆች ሥራቸውን እንደ አብዮት ሳይሆን እንደ ተሐድሶ ነበረ የቆጠሩት። ተግባራቸውንም በቤተ ክርስቲያን ላይ ወይም በታሪካዊ ክርስትና ላይ የተደራጀ አመጽ አድርገው አላዩትም።... ተግባራቸውን ቤተ ክርስቲያንን ወደ ቀደመው መልክና ወደ ቀደመው የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮት የመጥራት አድርገው ተመልክተውታል። አዲስ ነገር ለመፍጠርም አልሞከሩም። አዲስ መልክ ለመሥራት ሳይሆን ለማደስ፣ ቤተ ክርስቲያንን ወደ ቀደመው መሰረቷና ወደ መገኛዋ ለመጥራት ሞከሩ።"

__ሮበርት ስፕሮል

#ተሀድሶ_ይቀጥላል

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
863 viewsedited  06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 09:11:39 "ተሐድሶው ስለ ሉተር፣ካልቪን፣ ቲንደል፣ ወይም ስለ ሌሎች በፍፁም አይደለም። ተሐድሶው የክርስቶስን ወንጌል  በመመለስ፣ በመግለጽ ዳግም በሥራ ላይ ስለ ማዋል ነው። በሁሉም ትውልድ ውስጥ ተመሳሳይ መመለስ እና ገለፃ ያስፈልጋል። ተሐድሶ መቼም አያልቅም።"

       __ደስቲን ቤንጅ

#Happy_505th_Reformation_Day!!
October 31 1517

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.1K viewsedited  06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 15:15:46 "የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በተደጋጋሚና በግልፅ አንድ ነገር ያረጋግጥልናል። አንድ ጊዜ የቅዱሳት መጻህፍት የበላይነት በየትኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቅ፣ ቡድን፣ ቤተ እምነት ወይም ቤተ ክርስቲያን ከተተወ፣ በነገረ መለኮቱም ሆነ በተግባር ውስጥ ያለው የቁልቁለት ጉዞ የማይቀር ነው።"

__James white

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.1K views12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 07:49:01 መድረኩ የግል ምስክርነት፣ የፖለቲካዊ ንግግሮች፣ የቡድን ሕክምናዎች፣ የአበረታች ንግግሮች፣ የራስ አገዝ ምክሮች፣ የዓለማዊ ፍልስፍናዎች፣ ወይም የሳይንሳዊ ንድፈ ሐሳቦች የሚቀርቡበት ቦታ አይደለም። መድረክ የእግዚአብሔር ቃል ዙፋን ነው። ስለዚህ ቅዱስ ቃሉ በስብከቶች ቅድሚያ የሚሰጠው መሆን አለበት።

   __H.B. Charles Jr.

#Sabbath

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.0K views04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 00:18:07 የገነት ታላቁ መስህብ የዕንቁ ደጆቿ፣ የወርቅ ጎዳናዎቿ ወይም የመላእክት ዝማሬዎች ሳይሆኑ ክርስቶስ ነው።

__ዲ.ኤል. ሙዲ

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
544 viewsedited  21:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 10:57:04 ❝እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም።❞
—ኤፌሶን 2: 19
×××××××
በሃጢአታችን ምክንያት መላ ማንነታችን የተበላሸ እና ከእግዚአብሔር ክብር የጎደለ በመሆኑ ለእግዚአብሔር ጠላቶች ሆነን እንኖር ነበር። እግዚአብሔር ቃልኪዳን ካደረገላቸው እስራኤል በመራቃችን ደግሞ ከተስፋም ፈጽሞ ርቀን ነበር። ነገር ግን አሁን እኛ ራሳችን በመንፈስ እስራኤል ሆነን ከቃልኪዳን ማህበረሰብ ተቆጥረን የአንድ ሃገር ዜጎች ሆነናል። ዜግነታችንም ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ሠማያዊ ነው። አስደናቂው ነገር ይህ ብቻ አይደለም።የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሆነናል። ልጆች በመሆናችንም ወራሾች ተደርገናል። ስለዚህ 'ከእንግዲህ ወዲህ' ተብሎ ታሪክ ይጻፍልናል። ለዚህ ሁሉ ምክንያቱ አንዱ ቅዱስ በመስቀል ላይ የተቀበለው ስቃይ ነው።

__ተስፋጽዮን አለማየሁ (መጋቢ)

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.9K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 22:45:45 "የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ረቂቅ መርሆዎችን ብቻ ሳይሆን እውነተኛ የሥልጣን መስመሮችን ይመለከታል [ያካትታል]። እግዚአብሔር ትእዛዛትን የማውጣት፣ ግዴታዎችን የመጫን እና የሰዎችን ህሊና የማሰር መብት አለው።"

__ሮበርት ስፕሮል

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.3K viewsedited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 14:39:07 ስማኝማ! አንተ የዛልከው ሆይ!

"የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤...።" እብ. 12፡1_3

“ኢየሱስን ተመልክተን” የሚለው ሐረግ ከሩቅ በፊት ለፊት የመጀመሪያው መስመር ላይ ያለውን ተመልክተን ማለት ነው። እርሱ ደረሱብኝ ብሎ ስጋት ስለሌለው ሽምጥ አይሮጥም እንዲያውም ዞር እያለ "ሳብ" "በርታ" ነው የሚለው፣ የአሁን ቀጣይ ጊዜን የሚያሳይ “እየተመለከትን” በዚህ ሩጫ ላይ ቅጽል ስሙ “ፈጻሚውን” የሚል ነው። የእምነታችን ማረፊያ እምነታችን አይደለም፣ ከፊታችን ያለው ኢየሱስ ነው!

መቼም ግባ መቼ አንተ ማነህ ሲሉህ እኔ ከፈጻሚው ጋር ነኝ እያልክ ነው የምትገባው፣ ከእርሱ ጋር ሆኖ ሩጫውን የጨረሰ ከኋላ ሆኖ አንደኛ ነው።!!

_በሳምሶን ጥላሁን

#Sabbath

@Gospel_of_God @Gospel_of_God
@Gospel_of_God @Gospel_of_God
1.5K viewsedited  11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ