2022-07-05 14:40:03
አባቴ የት ነህ ?
#ይነበብ
------------------
እኔ ስሜ ሸዋነሽ ብዙአለም ተሰማ እባላለሁ የተወለድኩት አዲስ አበባ ቶታል ሶስት ቁጥር ማዞሪያ የእናቴ ስም ወ/ሮ ማናህሎሽ ዘሩ ትባላለች አባቴ ደግሞ ፶/አለቃ ብዙአለም ተሰማ ይባላል ።
እናቴና አባቴ በ1978 ዓ.ም ተዋዉቀዉ ከዛም እኔ ተወለድኩ አባቴ የቀድሞ የጦር ሰራዊት አባል ስለነበር ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ጎንደር አዘዞ ተቀይሮ ሄደ አዘዞ የጦር ካንፕ ዉስጥ በወቅቱ የወታደሮች ደሞዝ ከፋይ ነበር እና እኔም በአባቴ ተቆሬጭ ለተወሰነ ጊዜ እንዳደኩ አቃለሁ አባቴ እዛዉ አዘዞ ከተማ ቤተሰብ እንዳሉት የአባቴ ጓደኛ ከቅርብ አመታት በፊት ነግሮኛል እናቴ አሁን በህይወት የለችም እኔም ያለ እናትና ያለ አባት አድጌያለሁ እባካችሁ የአዘዞ ከተማ ማህበረሰብ ይህን ፁሁፍ የምታዩ በተለይ ከ1980-1983 ዓ.ም አዘዞ ካንፕ ዉስጥ የነበራችሁ አባቴን አገናኙኝ አባቴ በህይወት ባይኖር እንኳ የእሱን ዘመዶች ማግኘት እፈልጋለሁ ።
አባቴ የት ነህ ? እዉነት በህይወት ትኖራለህ ፈላጊ ልጅህ ወ/ሪት ሽዋነሽ ብዙአለም ተሰማ ከአዲስ አበባ ።
like comment share በማድረግ እንድትተባበሩኝ በፈጣሪ ስም እለምናችኋለሁ የአንድ ሰዉ ሼር ደስታ ይዞ ሊመጣ ይችላልና
ግርማ ሙሉ ከአዘዞና ልጆቿ ፔጅ የተገኘ !!
______
ሌሎችም የጠፋ ቤተሰብ መፈለግ የምትሹ በቴሌግራም ቻናላችን አድርሱን
https://t.me/tadiyossisay
3.3K views11:40