በፍላጎት መንገድ... በምኞት ጎዳና ፣ ስመጣ ተጉዤ ገንዘብ እየፈለግሁ... "ፍቅር ይበልጣል" የሚል ፣ ከንቱ ሙግት ይዤ እኔም ልክ እንዳንቺ... ከገንዘብ ወዳጅ ጋር ፣ ተከራክሪያለሁ ገንዘብ የማይገዛው... ብዙ ደስታ አለ ፣ ስል አስረድቻለሁ፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ግን ደሞ ግን ደሞ... በማስረዳቴ ውስጥ ፣ አለ የሚያስረዳኝ ከፍቅር ከገንዘብ... ከምንም የሚበልጥ ፣ "እውነት " ይሉት አዳኝ፡፡ ፡፡፡፡፡፡ እናም እውነት ማለት... በጭራሽ አይደለም! አንድድ እውነት ለማቆም ፣ አንዱን እውነት መጣል አትጠራጠሪ!!! አንዱ ገንዘብ ሲመርጥ ፣ አንዱ ፍቅር ይመርጣል አልጠራጠርም!!! ወይ ልብ ይወስናል ፣ ወይ አንጀት ይቆርጣል! "ሒድ"ወዳልሽኝ ልሒድ!!! በማይሆን ክርክር ፣ ማን እውነቱን ያጣል?! ሒጅ ወደ ፈለግሽው!!! ከፍቅር ከገንዘብ ፣ ፍላጎት ይበልጣል፡፡ ።።።። (በላይ በቀለ ወያ) https://t.me/poem_by_poem 1.5K viewsbelaya, 07:48