Get Mystery Box with random crypto!

ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Saints

የቴሌግራም ቻናል አርማ gedlekidusan — ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Saints
የቴሌግራም ቻናል አርማ gedlekidusan — ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Saints
የሰርጥ አድራሻ: @gedlekidusan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.61K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ገጽ ስለ ቅዱሳን ክብር ተዓምር ገድል ይናገራል::

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-24 16:30:43 እንኳን ለሰማዕታት ቅዱስ እንጣዎስ እና ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ወንድሞቻችሁ እና እህቶቻችሁ እንዲያነቡት ተጋሩት(share it)
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ

<3 ቅዱስ እንጣዎስ አሞራዊ <3

ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ አስቸጋሪ አረማዊ ነበር። ሃገሩ ሶርያ (ደማስቆ) ሲሆን ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር። በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል። በሥጋዊ ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው።

ሁልጊዜ በጠዋት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል። የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ አንድም ካህናትን ለመደብደብ ነበር። የሚገርመው ግን የወቅቱ ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም። ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ። ምክንያቱም ክርስትና ማለት ጠላትን መውደድ ነውና።
(ማቴ. ፯)

የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው አንድ ቀን ፍሬ አፈራ። እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል። ከዚያም እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ የሚማታውን ተማቶ የሚዘርፈውንም ዘርፎ የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት አቃጠላቸው።

እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም። "ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ እንጂ መሞቱን አይፈልግም። ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር እንደማያይ ዝም የሚለው። ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም።

እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል አልተሳካለትም። ከበሩ አካባቢ ሲደርስ ከወደ ሰማይ አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደ እርሱ ዓይነት ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጓቸው ተመለከተ።

ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ)። ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ። ላበቱ በግንባሩ ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ።

"ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ። ይቅር በለኝና ላምልክህ፤ ስምህንም ልሸከም።" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ አሰምቶ ጸለየ። በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን በምን እንደ ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው። እነርሱም የፈለጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና።

ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ። መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር በሉኝ?" አለ። ቀጥሎም ወደ ጳጳስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ።" ሲል ጠየቀ። እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር።

እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር። ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ ወደ ውኃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ ወረደ። ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከአሥር ሺህ በላይ አሕዛብ ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል።

ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በኋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ። ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን፣ ጸሎትን፣ ፍቅርን፣ ምጽዋትን ገንዘብ አደረገ። ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታዎት ሆነ። እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ ቅዱሳን ማኅበር (ኢየሩሳሌም) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች።

እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ።
አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት። "አይሆንም።" አላቸው። በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት።

ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው። ደሙና ጥርሶቹ መሬት ላይ ተዘሩ። ነገር ግን ይህ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም። አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው በዚህች ቀን ገድለውታል። ቅዱስ እንጣዎስም ከኋለኛው ዘመን ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል።

<3 ቅዱስ ያዕቆብ ግብጻዊ <3

ቅዱስ ያዕቆብ ተወልዶ ያደገው መኑፍ (ግብጽ) ውስጥ ሲሆን ዘመኑም ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው። ወላጆቹ የተባረኩ ናቸውና እርሱ ሳይወለድ የነበሯቸውን ሦስት ሴቶች ልጆች "ተማሩ" ብለው ወደ ገዳም ቢያስገቧቸው በዚያው መንነው ቀሩባቸው።

በዚህ ሲያዝኑ ቅዱስ ያዕቆብ ተወልዶላቸዋል። እነርሱም በቃለ እግዚአብሔርና በጥበብ አሳድገውታል። ትንሽ ከፍ ሲል በአካባቢው ከነበረ አንድ ቅዱስ ሽማግሌ ጋር ተደብቀው ገድልን ይሠሩ ነበር። ሁሌም መልካም ምግባራትን ከመፈጸም ባለፈ ሙሉውን ሌሊት ባሕር ውስጥ ሰጥመው ይጸልዩ ነበር።

ዘመነ ሰማዕታት በመጣ ጊዜም ሁለቱ ተመካክረው ስመ ክርስቶስን በገሃድ ሰብከዋል። በዚህ ምክንያት ቅዱሱን ሽማግሌ ወዲያው ሲገድሉት ቅዱስ ያዕቆብን ግን ብዙ አሰቃይተውታል። በመጨረሻም በዚህች ቀን ተሰይፎ የክብርን አክሊል ተቀብሏል።

አምላከ ሰማዕታት ቤተ ክርስቲያንን ከመከራ ይጠብቅልን። ከበረከታቸውም ያሳትፈን።

ነሐሴ ፲፯ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ተዝካረ ፍልሠታ ለማርያም ድንግል
፪.ቅዱስ እንጣዎስ አሞራዊ (ሰማዕት)
፫.ቅዱስ ያዕቆብ ግብጻዊ (ሰማዕት)
፬.ቅዱስ አክራጥስ ሰማዕት
፭.አባ እለእስክንድሮስ ዘቁስጥንጥንያ

ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ቀዳሜ ሰማዕት)
፪.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
፫.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
፬.አባ ገሪማ ዘመደራ
፭.አባ ጰላሞን ፈላሢ
፮.አባ ለትጹን የዋህ
፯.ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሊቅ (ዘደሴተ ቆጵሮስ)

"ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው። ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ። ስለዚህ ግን የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት በእርሱ ያምኑ ዘንድ ላላቸው ሰዎች ምሳሌ እንድሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ዋና በምሆን በእኔ ላይ ትዕግስቱን ሁሉ ያሳይ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ።"
(፩ጢሞ ፩፥፲፭-፲፮)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
471 views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:15:50
"እንዘ ይፀውረኪ በሐቂፍ ወይስዕመኪ በአፍ
አመ አፍለሰኪ ወልድ ውስተ የማኑ ለዐሪፍ
ጽጌ ዕፀ ገነት ማርያም ዘትጼንዊ ለአንፍ
እንዘ ይትጓድዑ አክናፈ በክንፍ
ለቀበላኪ ወረዱ አእላፍ"

(ለአፍንጫ መዐዛን የምትሰጪ የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ።)
(አባ ጽጌ ድንግል ወአባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ)
712 views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:12:10
"ፈለሰት ማርያም በስብሐት ውስተ ሰማያት መላእክት ወሊቃነ መላእክት ወረዱ ለተቀብሎታ"

(እመቤታችን በምስጋና ወደዚያኛው ዓለም በተለየች ጊዜ ለአቀባበሏ መላእክትና ሊቃነ መላእክት ወረዱ።)
(ቅዱስ ያሬድ)
691 views12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 20:37:49
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በዚችም ዕለት ዳግመኛ የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው። የሥጋውም ፍልሰት ከእመቤታችን ድንግል ማርያም የሥጋ ፍልሰት ጋር አንድ ሁኗልና ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥዕሉን ከሥዕሏ አጠገብ ይሥላሉ በስሙ ለሚማፀኑ የድኅነት ወደብ ይሆን ዘንድ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በኃያሉ ተጋዳይ በጊዮርጊስም ጸሎት በእኛ ላይ ምሕረት፣ ይቅርታ፣ ቸርነት ይሁን፤ ለዘላለሙ አሜን።

"ሰላም ለጊዮርጊስ ተውላጠ ፃማሁ ወሕማሙ።
እንተ ተለዓለ ሞገሰ ስሙ።
በፍልሰትኪ ድንግል ዘተቶስሐ ፍልሰተ ዐፅሙ።
እንዘ ይብል ሶበ ጸለየ ኀቤሃ ቀዲሙ።
ምስለ ፍልሰትኪ ደምርኒ እሙ።"

(ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ)
914 views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 20:34:51
646 views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 20:34:44 አምላከ ቅዱሳን ከድንግል እመ ብርሃን ፍቅር፣ ከጣዕሟ፣ ከረድኤቷ ያድለን። የወዳጆቿን ጊጋርና ጊዮርጊስን በረከትም ያብዛልን።

ነሐሴ ፲፮ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም (ፍልሠቷ፣ ትንሣኤዋና ዕርገቷ)
፪.ቅዱሳን ሐዋርያት
፫.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት (ፍልሠቱ)
፬.ቅዱስ ጊጋር ሶርያዊ (ሰማዕት)

ወርኀዊ በዓላት
፩.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
፪.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት)
፫.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮጵያ (የቅዱስ ላሊበላ ወንድም)
፬.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
፭.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
፮.አባ ዳንኤል ጻድቅ
፯.ቅዱስ አባ ዮሐንስ ጻድቅ (ወንጌሉ ዘወርቅ)

"ወደ ማደሪያዎቹ እንገባለን። እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን።
አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ። አንተና የመቅደስህ ታቦት።
ካህናቶችህ ጽድቅን ይልበሱ። ቅዱሳንህም ደስ ይበላቸው።
ስለ ባሪያህ ስለ ዳዊት....."
(መዝ ፻፴፩፥፯-፲)

"ወዳጄ ሆይ! ተነሺ። ውበቴ ሆይ! ነዪ።
..... በዓለት፣ በንቃቃትና በገደል መሸሸጊያ ያለሽ ርግብ ሆይ! ቃልሽ መልካም ውበትሽም ያማረ ነውና መልክሽን አሳዪኝ። ድምጽሽንም አሰሚኝ።"
(መኃ ፪፥፲-፲፬)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
661 views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ