Get Mystery Box with random crypto!

#ይወረሳሉ ! ' በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች #ይወረሳሉ ' - የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተ | Fast mereja

#ይወረሳሉ !

" በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች #ይወረሳሉ " - የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን

ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ርምጃ እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል።

በሕገወጥ መንገድ ገብተዋል የተባሉ መኪናዎችን የመለየት ሥራ መሰራት ከተጀመረ አንድ ወር ሆኖታል ተብሏል።

ባለሥልጣኑ ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ጥናት በባለሥልጣኑ የሚመዘገበው የገንዘብ መጠን እና ለገቢዎች ቢሮ የሚቆረጠው ደረሰኝ ተመሳሳይ ያለመሆን ሁኔታዎች መኖራቸው አመላክቷል።

በዚህም በተለይ የአዲስ ተሽከርካሪዎች ዋጋ የሚቆረጥበት ደረሰኝና ገዢዎች ለመኪናው የሚከፍሉት ዋጋ ሰፊ ልዩነት ያለው መሆኑ ተረጋግጧል።

መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ግዥና ሽያጭ ማግኘት የሚገባውን የታክስ ገቢ እያገኘ አይደለም ያለው ባለስልጣን መ/ቤቱ ይህንን እና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎችን የመለየት ሥራ ተጀምሯል ብሏል።

ተቋሙ በተለያዩ ጊዜያት ሁለት አይነት ሕገወጥ ተግባራት እንደሚያጋጥሙት ገልጿል እነዚህም ፦
- ከክልል በዝውውር የሚመጡ መኪናዎች ላይና
- በተጭበረበረ ሰነድ የተመዘገቡ መኪናዎች ናቸው።

ይህንን ለመከላከል የሚያግዝ ዘመናዊ ሥርዓት የመኪናዎቹን ሕጋዊነት የማጣራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አሳውቋል።

የማጣራት ሥራው የሚሠራው ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ ሲሆን ከዚህ በፊት አንድ የመኪና ሻጭ በስሙ የነበረውን መኪና ለሌላ ሰው ሲያስተላልፍ የማጣራት ሥራ እንዳልተሠራ እና በዚህም መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ታክስ እንዳላገኘ ተገልጿል።

አሁን ግን ከጉሙሩክ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን አዲስ ሥርዓት መዘርጋት ተችሏል ተብሏል።

ሥርዓቱም መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ማግኘት የሚገባውን ታክስ እንዲያገኝ ከማድረግ ባለፈ መኪና ገዢዎች እንዳይጭበረበሩ እና መንግሥት ሕገወጥነትን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት የሚያጠናክር እንደሆነ ተገልጿል።

በሂደቱም በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች #እንደሚወረሱ ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ፤ የአዲስ መኪና ገዢዎች የሚከፍሉት ዋጋ በደረሰኙ ላይ መጠቀሱን በማረጋገጥ ሊገዙ ይገባል ብሏል።

ይህንን ማድረግ ለገዢው በርካታ ጠቀሜታ የሚያስገኝ ከመሆኑ ባለፈ የሚሰበሰበው ገቢ ለከተማዋ መሠረተ ልማት የሚውል በመሆኑ በኃላፊነት ሊታይ እንደሚገባ አሳስቧል።

#ኢፕድ