2023-04-20 19:00:44
1) ዒድ አልፈጥር ዛሬ ማታ ጨረቃ ከታየች ነገ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል። የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት፤ የ2015 የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሐሙስ ማታ ከታየች ነገ፣ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ እንደሚከበር አስታውቋል። የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት የ2015 የዒድ አልፈጥር በዓል አከባበርን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ በመግለጫውም 1 ሺሕ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ሕብረተሰብ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን አስተላልፏል። ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ ማቅረቡ ተገልጿል።
2) መንግሥት በሱዳን ባለው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዋናው መስሪያ ቤት እና ካርቱም በሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ አማካኝነት የኢትዮጵያውያንን ደኅንነት ለመጠበቅ እየሠራ መሆኑን ገልጿል፡፡ የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና አጎራባች ክልሎች አባል የሆኑበት ግብረ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ መቋቋሙም ተመላክቷል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስፈላጊ መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚያሳውቅ አመላክቷል።
3) የጉሙሩክ ኮሚሽን በኮንትሮ ባንድ ንግድ ላይ የጸጥታ አካላት እጃቸው የረዘመ በመሆኑ የኮትሮ ባንድ ንግድ መቀነስ አልተቻለም ሲል አስታወቋል፡፡ በፀጥታ አካላት የሚደግፉት የኮንትሮባንድ አሳላፊዎችና ነጋዴዎች ቁጥራቸው እየተበራከተ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ ባለፉት ስምንት ወራቶች ውስጥ ሁለት ኮኖኔሎች እና ሌሎችም የክልል የጸጥታ አካላት በኮንትሮባንድ ንግድ ተሳትፈው መያዛቸው ተገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ በተያዘው በበጀት አመቱ ስምንት ወራቶች ውስጥ 5 ቢሊዮን ብር ከኮንትሮ ባንድ ንግድ ማዳን እንደተቻለ ገልጿል።
4) የሱዳን ቀውስ በጎረቤት አገራት ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሆነ ምሁራን አመላክተዋል። ምሁራኑ ‘’የቀይ ባህር መስመር የዓለም መሠረታዊ የንግድ መስመር እንደመሆኑ፤ ሱዳንም ትልቅ ሃገር ከመሆኗ አንጻር ለአጭርም ሆነ ለረዥም ጊዜ ግጭት መፈጠሩ ለቀጠናው ከፍተኛ የሆነ ስጋት እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። በተለይ በኢትዮጵያ የሚኖረው ተፅዕኖ የጎላ ሊሆን እንደሚችል አመላክተው፤ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር በተያያዘና ሁለቱ አገራት በድንበር ከመተሳሰራቸውም በላይ፤ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሱዳን ውስጥ መኖራቸው፤ የሀገራቱን ትስስሮሽ የጠነከረ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
5) ሩሲያ ሰሜን ኮሪያን ልታስታጥቅ እንደምትችል አስጠንቅቃለች። አሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን ዘመናዊ የጦር መሳሪያ በማስታጠቅ ላይ መሆናቸው ይታወሳል። አሜሪካ ወዳጅ የምትላቸውን ሀገራት በማግባባት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንዲለግሱ በማድረግ ላይ ስትሆን፤ በዚህም ደቡብ ኮሪያ ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንድትሰጥ ማግባባቷ ተገልጿል። ደቡብ ኮሪያም ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ለመስጠት ሁኔታዎችን እየገመገመች መሆኑን ከሰሞኑ አስታውቃለች። ሩሲያ ባወጣችው መግለጫ ደቡብ ኮሪያ ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንዳትሰጥ አስጠንቅቃ፤ ደቡብ ኮሪያ የሩሲያን ማስጠንቀቂያ ችላ ብላ ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ከሰጠች፤ ሩሲያ በአፀፋው ለሰሜን ኮሪያ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ እንደምታስታጥቅ ገልጻለች።
ቴሌግራም : https://t.me/world_info1
893 views🅐🅑🅓🅨, 16:00