Get Mystery Box with random crypto!

አለምነህ ዋሴ ከሳምንት በፊት 'ሀዘኔን ምገልጸው አሁን ለሞቱት አይደለም። ቀጥሎ ለሚሞቱት ነው ሀዘ | ፋሲል ከነማ (አፄዎቹ) እግር ኳስ ክለብ / Fasil Kenema Football Club ™🇦🇹

አለምነህ ዋሴ ከሳምንት በፊት
"ሀዘኔን ምገልጸው አሁን ለሞቱት አይደለም። ቀጥሎ ለሚሞቱት ነው ሀዘኔን ምገልጸው። በቁም እየሰሙ ለሚሞቱት ማለት ነው። ምንም የተለወጠ ሁኔታ የለም። the same thing እነዚህ ሰዎች ደሙን ጠርገው ወደ እርሻ ወደ ሱቅ ይሄዳሉ፡ until it happens again፡ አሁን እነሱ ናቸው በቁም እያሉ የማዝንላቸው፣ የሚሰሙኝ። እንደወንድም እንደወገን በጣም አዝናለው" ብሎ ነበር።

(አሁን ጥያቄው ቋሚውን እንዴት እናድነው ነው? ከምኑም ውስጥ የሌሉ ንፁሃን በማንነታቸው እየተጨፈጨፉ የመፍትሄ ያለህ! ማለት የለብንም? በሀገራችን ላይ ይህ ነውር ሲፈፀም መፍትሄ መጠየቅ የለብንም? እየሞተ ያለው ክቡር የሰው ልጅ ነው። ኢትዮጵያዊ ውድ ወገናችን ነው።

ይህን የምፅፈው መፍትሄ በጋራ እንድንፈልግ ነፍሴ ስቅዝ አድርጋ ስለያዘችኝ ነው። እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ ስለታመምሁ ነው። ለሀገሬም ስለምሰጋ ነው። ለአማራ ያልሆነች ሀገር ለማናችንም አትሆንም። ኢትዮጵያ እዚህ ደረጃ መድረሷ ያሳዝናል። አስቸኳይ መፍትሄ ያስፈልጋል።

ምን ተሻለን?

ክልሎች ልዩ ሀይላቸውን ልከው የወለጋን አማራ ይጠብቁ፣ ወይ ወደ ሌሎች ክልሎች ይጓጓዙ፣ ወይ ሁሉም ይታጠቁና አልሞትባይ ተጋዳይ ይሁኑ፣ ወይ ወደ ጎሮቤት ሀገራት ይሰደዱ፣ ወይ የተባበሩት መንግስታት ይረከበን፣ ወይ በቁማቸው አሁኑኑ RIP እንበላቸው? መፍትሄ )