Get Mystery Box with random crypto!

ፋሲል ከነማ (አፄዎቹ) እግር ኳስ ክለብ / Fasil Kenema Football Club ™🇦🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ fasilkenema_sc_official — ፋሲል ከነማ (አፄዎቹ) እግር ኳስ ክለብ / Fasil Kenema Football Club ™🇦🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ fasilkenema_sc_official — ፋሲል ከነማ (አፄዎቹ) እግር ኳስ ክለብ / Fasil Kenema Football Club ™🇦🇹
የሰርጥ አድራሻ: @fasilkenema_sc_official
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.59K
የሰርጥ መግለጫ

ወቅታዊ የሆኑ
#ዜናዎች
#ዝዉዉሮችን
እንዲሁም
#የቀጥታ ስርጭት
አስተያየት ለመስጠት እና ለጥቆማ
➠ @empair_bot
አንጋፋውና ተወዳጁ ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ በ1960 ዓ/ም ተመሰረተ። ይህ አንጋፋ የአፄዎች ክለብ 55 አመታትን አስቆጥሯል፡፡
#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም በላይ ነው!!

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 12:42:40
ሱራፌል ዳኛቸው በአንድ ወቅት ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረገው ቆይታ እንዲህ ብለው ጠይቀውት ነበር

ሱራፌል በየትኛው አጨዋወት ቢጫወት ይመርጣል። በመስመር አጥቂ፣ ከአጥቂ ጀርባ ወይስ የአማካይ ስፍራ ?
አዳማ እያለሁ መስመር አጥቂ ነበርኩ። ከቀኝ መስመር እየተነሳው ወደ ግራም መስመር እየቀያየርኩ ነው የምጫወተው። አንዳንዴ አማካይ አድርጎ አሰልጣኝ አሸናፊ ያጫውተኝ ነበር። አሁን ፋሲል ነፃ ሚና ነው የተሰጠኝ፤ ከአጥቂ ጀርባ መጫወትን። ይህ ደግሞ በጣም ጠቅሞኛል። አንደኛ ጎል አስቆጥራለው ሁለተኛ የሚመለሱ ኳሶችን ከርቀት የመምታት አጋጣሚን አገኛለሁ። ሦስተኛ ሳልቆም ሜዳውን ሁሉ ሸፍኜ እንድጫወት ስለሚያደርገኝ በመስመር ከመጫወት ይልቅ ከአጥቂ ጀርባ በነፃ ሚና ተሰቶኝ መጫወትን እመርጣለው። ''ሱራ ነብሮ ''
ሼር አድርጉ



#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
522 views09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 12:40:59
#መድመቂያችን



#የአፄዎቹ_ቤተሰብ_ይሁኑ
ግሩፕ
@fasilyene



#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
470 views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 12:39:57
#ፋሲል_ከነማ ስፖርት ክለብ አሰልጣኝ መንተስኖት ጌጡን አስፈርሟል!!

ፋሲል ከነማ በ2015 የውድድር አመት ተጠናክሮ ለመቅረብ የአሰልጣኝ አባላቶችን በአዲስ መልክ አዋቅሯል!! የዋና አሰልጣኝ ሀላፊነት ለኃይሉ ነጋሽ የተሰጠ ሲሆን ም/አሰልጣኝ ሙሉቀን አቡሃይ ፣ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ አዳም ባዘዘው ሲሆኑ በፋሲል ከነማ የአካል ብቃት አሰልጣኝ በመሆን ወደ ቤቱ የተመለሰው ምንተስኖት ጌጡ ለሁለት አመት የሚያቆየው ውል በዛሬው እለት በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፀድቋል።

ፋሲል ከነማ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ሲያድግ በምክትል እና ዋና አሰልጣኝነት ሚና ያሳለፈው ምንተስኖት ጌጡ በአካል ብቃት የአሰልጣኝነት ሙያ የአሰልጣኝ አባሉን መቀላቀሉ ትልቅ ድጋፍ የሚሰጥ ነው!!

አሰልጣኝ ምንተስኖት ጌጡ እንኳን ደህና መጣህ መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንልህ እንመኛለን!!



#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
476 views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:31:52
የመጀመሪያው ጋምቢያዊ የፋሲል ከነማ ተጫዋች አጥቂ #ጋራይ_ጆፋን

#ማሊ ፣ #አይቬሪኮስት ፣ #ኡጋንዳ #ናይጄሪያ ፣ #ኬንያ ፣ #ቶጎ የነዚህ ሀገር ዜጎች የክለባችንን ማልያ ለብሰው ተጫውተዋል



#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
625 views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:45:03 የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ (ቲጋና) ከፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ገጽ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

*ፋሲል ከነማ፦ ጤና ይስጥልኝ ኃይሉ ነጋሽ የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ሆነህ በመሾምህ እንኳን ደስ አለህ እያልኩ ቡድኑን በሀላፊነት በመረከብህ ምን ተሰማህ? ፊርማህ ለአንድ አመት መሆኑ የእግር ኳስ ሀሳብን ለመተግበር የሚፈጥረው አሉታዊ ተፅዕኖ አለ??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ እንኳን አብሮ ደስ አለን!
ቡድኑን በሀላፊነት በመረከቤ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል። ምክንያቱም ፋሲል ከነማ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራነቱን በዋንጫ ክብሮች ያጀበ ለተከታታይ አመት በአፍሪካ መድረክ ሀገር የወከለ ከምስርታው ጀምሮ ትልቅ በሆነ ክለብ እና ክለቡን የህይወታቸው አካል አድርገው በሚደግፉ ደጋፊዎች ባሉበት ሁኔታ ሀላፊነት ወስዶ መሰራት ያስደስታል።
ሲቀጥል ከልጅነት እስከ እውቀት ላሳደገኝ ክለቤ ከተጫዋችነት ጀምሮ አሁን ደግሞ በአሰልጣኝነት መስራት ክብርም ኩራትም ነው እያልኩ የፊርማ አመት መብዛትና ማጠር ሳይሆን በምታስመዘግበው የስኬት ስራህ ነው ቀጣይነትህ የሚረጋገጠው እኔ ደግሞ ለክለቡ አዲስ ሰው ስላልሆንኩ ተፅዕኖ የለብኝም።

*ፋሲል ከነማ፦ ቡድኑን በዋና አሰልጣኝነት በስምምነት ከተረከብክ በኋላ ለ2015 የውድድር አመት ዝግጅት ጀምራችኋል ከጀመራችሁ ስንት ጊዜ ሆናችሁ?? ዝግጅታችሁስ በምን አይነት ሁኔታ እየሄደ ይገኛል።

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ ለ2015 ውድድር ዝግጅት ከጀመርን 23 ቀን አስቆጥረናል። የቡድናችን ስኳድ ተሟልቶ ልምምድ ለመጀመር ያልቻልንባቸው ሁኔታዎች የተጫዋቾች ጉዳት እና ለብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት ለመስጠት በሄዱ ልጆች እንዲሁም በሀገር ውስጥ የአጥቂ ቦታ ተጫዋች ለማስፈረም ያደረግነው ጥረት ባለመሳካቱ የውጭ ሀገር ተጫዋች ለማስፈረም ሂደቱ ጊዜ በመውሰዱ ልጆችን አሟልቶ ዝግጅት ለመስራት ብንቸገርም ባሉት ልጆች ዝግጅታችን በተገቢው መንገድ እየሰራን መጠናል አሁንም ጉዳት የተመለሱትን አዲስ ክለባችን የሚቀላቀሉትን እየጨመርን ልምምዳችን በቀን ሁለት ጊዜ በሜዳ ላይ እና በጅምናዚየም እየሰራን እንገኛለን።

*ፋሲል ከነማ፦ የአፄዎቹን ቡድን በ2015 የውድድር አመት በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እና በፕሪሚየር ሊጉ በአሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ ስር በምን አይነት የእግር ኳስ ሀሳብ እና አቀራረብ እንጠብቀው??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ በእርግጥ ፋሲል ከነማ ከ 2011 ዓ.ም ጀምሮ የራሱ የሆነ ቅርፅ የጨዋታ መንገድ ያለው ቡድን ነው። ሆኖም አሁንም ቢሆን የያዝናቸውን ተጫዋቾች ጥራት መሰረት አድርገን ኳስን ተቆጣጥሮ የሚጫወትና ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የጎል ክልል የሚደርስ ቡድን ለመሰራት ጥረት እያደረግን ነው።

*ፋሲል ከነማ፦ በተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ክለባችን ለዋንጫ ክብር ሲበቃ ወሳኝ ሚና ከነበራቸው ተጫዋቾች ጋር ተለያቶ አዳዲስ ልጆች አስፈርመናል ይሄ የቡድን ግንባታ እንዴት ይገለፃል??
ለእግር ኳስ ሀሳብህ መተግበሪያ የሚሆኑ ተጫዋቾችን አሟልተናል ብለህ ታምናለህ?? ከዚህ በኋላስ የተጫዋች ግዥ ይሆረናል??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ በእርግጥ ለ2015 እቅዳችን ይህ አልነበረም አብዛኛው የክለባችን ተጫዋቾች ውላቸውን የጨረሱ ስለነበሩ መቆየት ያለባቸውን በማቆየት ክፍተት አለብን ብለን ባሰብናቸው ቦታዎች ብቻ ጨምረን መጓዝ ነበር እቅዳችን...አስፈራሚ ኮሚቴዎች ውላቸውን ጨርሰው የምንፈልጋቸውን ልጆች ማቆየት እንዲቻል ከፍኛ ጥረት ቢያደርጉም በተለያዩ ምክኒያቶች አልተሳካም ሆኖም ተጫዋቾች ክለቡን ጠቅመዋል እነሱም ተጠቅመዋል ነገር ግን ማንንም ተጫዋች ያለፍላጎቱ ማቆየት አንፈልግም አዲስ የተቀላቀሉን ተጫዋቾች ክለባችንን የሚመጥኑ ስለሆኑ የተሻለ ነገር እንሰራለን ብለን እናምናለን። የተጫዋች ግዥን በተመለከተ አሁን ባለን ስኳድ ደስተኞች ነን ነገር ግን ፋሲልን ሊመጥን ይችላል ብለን ያመንበት የአጥቂ ቦታ ተጫዋች ካለ ወደፊት የምናየው ይሆናል።

*ፋሲል ከነማ፦ ከታዳጊ ቡድኑ ያደጉ አዲስ ተጫዋቾች አሉ? ከዚህ በፊት ያደጉትን ወጣቶች እድል መስጠት ላይ ምን ታስቧል?? የቡድናችን ስኳድ ጥልቀት እንዴት ነው??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ ለአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ጨዋታ ያስፈልጉናል ብለን ያመንባቸውን ልጆች ብቻ ነው ወደ ዝግጅት ይዘን የገባነው ነገር ግን ዘንድሮም ልክ እንደሁልጊዜው ከታዳጊ ቡድኑ የሚመጡ ተጫዋቾች ይኖራሉ ያንንም የምናደርገው የዚህን የደርሶ መልስ ጨዋታ ካደረግን በኋላ ወደ ቡድኑ ተቀላቀለው አብረው ይሰራሉ። የቡድናችን ስኳድ ከአምናው የተሻለ ይሆናል ብለን እናምናለን በሁሉም ቦታዎች ላይ አማራጮች አሉ በዛላይ ከታዳጊዎቻችን ትልቅ ጥረት እና መሻሻል እንጠብቃለን እድሉን ለማግኘት ጠንክረው መስራት ይጠበቅባቸዋል።

*ፋሲል ከነማ፦ የአሰልጣኝ አባላቶችህ እገዛ እንዴት ነው? የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ጨዋታ እየደረሰ ነው የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ እና ዝግጁ ለመሆን ምን እየተሰራ ነው??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ በእውነት ነው የምልህ የፋሲል ጥንካሬ ዋናው ስታፉ ነው። ሁሉም ክለብ እንዲኖረው የሚመኘው ሊኖረውም የሚገባ በጣም ጠንካራና ቀና የሆነ ስራህን በሙሉ የሚያቀልልህ ይቻላል እንጂ የማይቻል ነገር የለም ብሎ የሚያሰብ ትልቅ የሆነ የቡድን መሪ ይዘህ ካዛም አለፍ ስትል ይሄ የአንተሰራ ነው ይሄ የእኔ ሰራ ነው የማይባባል ሰታፍ ይዘህ እንዴት ውጤታማ አትሆንም ይሄ ነው የእኛ ትልቁ የውጤታችን ሚስጢር!! ይሄ መተሳሰብና የስራ ፍላጎት ተጫዋቾች ላይ በመወረዱ ውጤታማ እንድንሆን አድርጎናል፡፡

የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ጨዋታችን እየደረሰነው ቢያንስ ከዚህ በኋላ 10 ቀናቶች ይቀራሉ ሥራችንን በአግባቡ እየሰራን ነው ነገር ግን ትልቁ ችግራችን የወዳጅነት ጨዋታዎችን አለማድረጋችን ነው። ቀደም ብለው ዝግጅት ከጀመሩ ክለቦች ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን ለማድረግ ጥረት እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን እዚሁ ባህር ዳር ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ለመጫወት ሞክረናል ወደፊትም ለማድረግ ፕሮግራም ይዘናል ይሄ በቂ ነው ብለን አናስብም ባሉት ቀሪ ቀናቶች ውስጥ አንድም ጨዋታ ቢሆን ከተሻለ ቡድን ጋር ለማድረግ ጥረት እናደርጋለን።

*ፋሲል ከነማ፦ ከፋሲል ከነማ ቦርድ አመራሮች እና ደጋፊዎቻችን ምን አይነት እገዛ ትጠብቃለህ??

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ፦ የክለቡ ቦርድ አመራሮች አቅማቸው በፈቀደ መጠን መስራት ያለባቸውን እያደረጉ ነው ያለው ከዚህ በላይ ክለባችን ለማጠናከር ትልቅ ስራ እንደሚጠብቃቸው እያመንኩ ቡድኑን ለመገንባት በሰሩት ስራ ላቅያለ ምስጋና አለኝ።
ስለ ደጋፊው ምን እንደምልህ አላቅም የውጤታቸን ትልቁ እና ዋናው ተመስጋኝ ደጋፊዎቻችን ናቸው!! ክለባችን እንዲጠናከር ከመፈለግ አንፃር በዝውውር ወቅት ምን ያህል ጭንቀት እንደነበር ሁላችንም ተረድተነዋል አሁንም ቢሆን ቡድኑን የሚያውቁ አብዛኛውን ነባር ተጫዋቾችን ይዘን በመቀጠላችን ከአምናው የተሻለ ቡድን እንዳለን ተረድተው የተሻለ ነገር እንድንሰራ እንደተለመደው የማያራቋርጥ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጥሪየን አስተላልፋለሁ።

ፋሲል ከነማ፦ ለነበረን ቆይታ እናመሰግናለን!!

*አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ (ቲጋና)እኔም ከልብ አመሰግናለሁ።



#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
647 views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:43:36
አፄዎቹ

ልጆቻችን ስራ ላይ ናቸው 




#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
603 views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 14:26:32
#Leader
#captain
#emperor
#great_fan
#ሳኛ


#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
580 views11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:29:59
#ፋሲል_ከነማ ስፖርት ክለብ አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽን በዋና አሰልጣኝነት ሹሟል!!

ኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ክለባችን ፋሲል ከነማ ከቀድሞ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር በስምምነት ከተለያየ በኋላ በምክትል አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ (ቲጋና) እየተመራ በጥሩ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ገብቶ ከመሪው ክለብ ጋር የነበረውን ሰፊ የነጥብ ልዩነት በማጥበብ የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ በአስደናቂ ሁኔታ ማገባደዱ የሚታወስ ሲሆን የክለባችን የቦርድ አመራሮች በክለባችን ውስጥ በምክትል አሰልጣኝነት ለአራት አመት በማሳለፍ ያገለገለውን ባለብሩህ ተስፋ ሰጭ ወጣት አሰልጣኝ ለአንድ አመት በሚያቆይ ስምምነት በዛሬው እለት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውሉን አፅድቋል።

ፋሲል ከነማ በምክትል አሰልጣኝነት ሚና ሙሉቀን አቡሃይን ያስቀጠለ ሲሆን ክለባችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ ሲያድግ የአሰልጣኝ ዘማርያም ምክትል የነበረው እና ከዛም በዋና አሰልጣኝነት አፄዎቹን የመራው አሰልጣኝ ምንተስኖት ጌጡ ደግሞ የአካል ብቃት አሰልጣኝ በመሆን የአሰልጣኝ ቡድኑን የቀላቅሏል።

ከዋና አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ (ቲጋና) ጋር ስለ 2015 አመት የውድድር አመት የጨዋታ አቀራረብ፣ ስለ አፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ጨዋታ አጠቃላይ ዝግጅት ምን እንደሚመስል ያቀረብነውን መጠይቅ ከዝግጅት ምስሎች ጋር በቅርቡ ይዘንላችሁ እንቀርባለን።

#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው


@fasilkenema_sc_official
751 views18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 16:36:38
#ፋሲል_ከነማ ጋምቢያዊ ዜግነት ያለውን አጥቂ አስፈርሟል!!

በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ክለባችን ፋሲል ከነማ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን የሚወክል ሲሆን ለቀጣይ የ2015 አመት የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ቡድኑን ለማጠናከር አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ ቀደም በቃል ደረጃ ከስምምነት ደርሶ የነበረውን ጋምቢያዊ ዜግነት ያለውን አጥቂ በዛሬው ዕለት የግሉ አድርጓል፡፡

ፋሲል ከነማ ያስፈረመው አጥቂ ጋራይ ጆፋን ዜግነቱ ጋምቢያዊ ሲሆን እድሜው 24 ቁመቱ 1-82 ሲሆን በሀገሩ ጋምቢያ የጀመረው የእግር ኳስ ህይወቱ በእስራኤል እና ጆርጂያ ክለቦች ቀጥሎ በጥሩ አቋም ላይ እንዳሳለፈ መረጃዎች የሚገልፁ ሲሆን #ጆፋን ወጣት ፣ ፈጣን እና ባለክህሎት ተጫዋች በመሆኑ በክለባችን ውስጥ ትልቅ ግልጋሎት እንደሚሰጥ ታምኖበት ለአንድ አመት በሚያቆይ ውል ፈርሟል።

#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው

@fasilkenema_sc_official
762 views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 16:08:06 የቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ

ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ 0-0 ሩዋንዳ

➝ የመልሱን ጨዋታ ነሐሴ 29/2014 ሩዋንዳ ላይ ይደረጋል።
660 viewsedited  13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ