አብዱልፈታህ አልሲሲ የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን ለ3ኛ ጊዜ አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ የግብፅን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ለ3ኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
በዚህም አል ሲሲ ግብፅን ለቀጣይ 6 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት ያገለግላሉ ነው የተባለው፡፡
የግብፅ ብሔራዊ ምርጫ ባለስልጣን እንዳስታወቀው÷ በ2024 የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት አብዱልፋታህ አል ሲሲ 89 ነጥብ 6 በመቶ ድምፅ በማግኘት ለ3ኛ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
https://www.fanabc.com/archives/227223